(1) ነቀፋ የሌለበት
ፖስተሩ በክፉ ስራ ጥፋተኛ መሆን የለበትም። ፓስተሩ ትክክል የሆነን ነገር እያደረገ ካልሆነ ሌሎች መልካም እንዲያደርጉ መምራት አይችልም። ፓስተሩ ወጥ የሆነ የክርስትና ሕይወትን በተወሰነ ጊዜ ውስጥ ያሳየ ሰው መሆን አለበት። ይህ አስፈላጊ የሆነው በማኅበረሰቡ ውስጥ ጥሩ ምስክርነት እንዳለው ቤተክርስቲያን እንድታምንበት ነው።
ቤተክርስቲያን ለረጅም ጊዜ ባልተቋቋመበት ቦታ ፓስተሩ ለረጅም ጊዜ ክርስቲያን ላይሆን ይችላል። እሱ ሁሉም የብስለት ባህሪያት ላይኖሩት ይችላል ነገር ግን ለእግዚአብሔር የተሰጠን ሕይወት ማሳየት አለበት። ስህተቶቹን አምኖ የራሱን ባህሪ ለማስተካከል ፈቃደኛ መሆን አለበት።
ለብዙ አመታት በእስያ ውስጥ ያለ አንድ ፖስተር በአንድ መንደር ውስጥ ጌታ በሀይል ይጠቀምበት ነበር። ስኬቱ ለትዕቢት እና መንፈሳዊ ግዴለሽነት ዳረገው። አንድ ምሽት ላይ አንዲት ወጣት ሴት በሞተር ሳይክሉ አብራው እንድትሄድ ጠየቀች። ፈተና እንደሚፈጥርበትና በማኅበረሰቡ ዘንድ ያለውን ስም ሊያጠፋ እንደሚችል ቢያውቅም በሞኝነት ተስማማ። አባላቱ ስለ ድርጊቱ ሲያውቁ በቅንነቱ ላይ ያላቸውን መተማመን አጥተዋል። በመጨረሻም አገልግሎቱን መልቀቅ ነበረበት። በእግዚአብሔር ፀጋ ይህ ፓስተር በእግዚአብሔር ፊት እና እርሱ በጎዳቸው ሰዎች ፊት ራሱን አዋረደ። የመንፈሳዊ የበላይ ተመልካቹን ተግሣጽ ተቀበለ። ቀስ በቀስ ተአማኒነቱ እንደገና ተመለሰ እና የአገልግሎቱ ውጤታማነት ጨመረ።
► መሪ የማይታመን ከሆነ ምን ይፈጠራል?
(2) የአንድ ሚስት ባል የሆነ
በብዙ የዓለም ክፍሎች ከአንድ በላይ ማግባት የተለመደ ልማድ ነው። የእግዚአብሔር ንድፍ ለአንድ ሰው አንዲት ሚስት እንዲኖረው ነው። ፖስተሮች ምሳሌ መሆን አለባቸው። ይህ መስፈርት ፓስተሩ ጥሩ ባል ለመሆን የተቻለውን ሁሉ ማድረግ እንዳለበት ያመለክታል። ለሚስቱ ታማኝ እና አፍቃሪ መሆን አበት።
[1] (3) ቁም ነገረኛ
ፖስተሩ ስለ አገልግሎቱ ቁምነገረኛ መሆን አለበት። ውሳኔዎችን በፍጥነት ወይም በስሜት የሚወስን ስሜታዊ ሰው መሆን የለበትም። አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ በረጋ መንፈስ ማሰብ መቻል አለበት። በግል ጉዳዮች፣ በመዝናኛዎች ወይም ፈተናዎች አእምሮው ከአገልግሎቱ እንዲዘናጋ መፍቀድ የለበትም።
(4) ጥሩ ባህሪ ያለው
ፓስተሩ ስርዓት ያለው ባህሪ ሊኖረው ያስፈልጋል። አላስፈላጊ በሆነ መንገድ ባህሪ ሊኖረው አይገባም። ባህሪው ከሚያስተምራቸው የእግዚአብሔርን መምሰል ሥርዓቶች ጋር የሚስማማ መሆን አለበት።
አንድ ፖስተር ለሚያገለግልበት ቦታ ልማዶች አክብሮት ማሳየትን መማር ይኖርበታል። አንድን ሰው ያስቀየመ ስህተት እንደሰራ ከተገነዘበ ትሁት ሊሆንና ይቅርታ ሊጠይቅ ይገባል።
(5) እንግዳ ተቀባይ
እንግዳ ተቀባይ መሆን ማለት የተጓዥ ሰውን ምግብ፣ ማረፊያ እና የሚያስፈልገው ፍላጎቶች ማሟላት ማለት ነው። ፓስተሩ ለሌሎች ሰዎች ፍላጎቶች ምላሽ የሚሰጥ ሰው መሆን አለበት። ለማካፈል ፈቃደኛ መሆን አለበት። እርሱ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሚያገኛቸው ሰዎች እንኳን ሳይቀር ተግባቢ እና አጋዥ መሆን አለበት።
► ይህ ብቃት ለመሪ ለምን አስፈላጊ ይሆናል?
(6) ማስተማር የሚችል
ፖስተሩ ሰዎች መረዳት ይችሉ ዘንድ እውነትን መግለፅ መቻል አለበት። እራሱን የማስተማር እና የማንበብ ሃላፊነት መውሰድ አለበት።
(7) የማይሰክር
ፖስተሩ በወይን ጠጅ ተፅዕኖ ስር ለመሆን መፍቀድ የለበትም። ባህሪው በአልኮል የተጠቃ ሰውን መምሰል የለበትም። ይህ መርህ ተመሳሳይ ተፅዕኖዎችን ለሚያሳድሩ ሌሎች ንጥረነገሮችንም ይመለከታል።
(8) ፀበኛ ያልሆነ
ፓስተሩ በኃይል ዛቻ ነገሮችን ለማግኘት መሞከር የለበትም። ቅር ያሰኘውን ሰው ለመጉዳት ዝግጁ መሆን የለበትም። (2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥24-25 ተመልከቱ።)
► ለፖስተር ትክክለኛውን ቁጣ ለማሳየት ምን አይነት መንገዶች ይኖራሉ?
(9) ስግብግብ ያልሆነ
ጠበቆች፣ ሻጮች፣ ፖለቲከኞችና ሌሎች ተመሳሳይ ሥራ ያላቸው ሰዎች ሰዎችን ለማስደሰት ሲሉ እውነትን ወደ ጎን ለመተው ይፈተናሉ። ፖስተርም በተመሳሳይ ይፈተናል ምክንያቱም የእግዚአብሔር ቃል እውነት ሁሉንም ሰው አያስደስትም። ፓስተር በገንዘብ ቢጠቅመውም ባይጠቅመውም ለእውነት ታማኝ መሆን አለበት።
አንድ ፓስተር የቤተክርስቲያን አገልግሎት በገንዘብ ሲደገፍ ለማየት መፈለግ አለበት። ሁልጊዜ ምን ሊሰጡት እንደሚገባ ከማሰብ ይልቅ፤ አንድ ቤተሰብ አባላቱን እርስ በእርስ እንደሚንከባከብ ቤተክርስቲያኗን እንዲሁ መምራት አለበት።
(10) ቤቱን በደንብ የሚያስተዳድር
የፖስተሩ የመሪነት ችሎታ በቤት ውስጥ መታየት አለበት። ልጆቹን መቆጣጠር አለበት። የራሱን ቤት መምራት ካልቻለ ቤተክርስቲያንን መምራት አይችልም። ልጆቹ ፍፁም ባህሪ ሊኖራቸው ይገባል ማለት ሳይሆን ፓስተሩ በታማኝነት እየመራቸው እና እያስተካከላቸው ነው ማለት ነው። ይህ አዋቂ የሆኑና እና ከስልጣኑ የራቁ ልጆችን አያካትትም ምክንያቱም እርሱ አሁንም ለእነርሱ ተጠያቂ አይደለም።
(11) አዲስ አማኝ ያልሆነ
አንድ ሰው በፍጥነት በስልጣን ላይ ከተቀመጠ በትዕቢት ይፈተናል። ሰይጣን እንዲወድቅ ያደረገው ሀጥያት ትዕቢት ነው። ዕድገት ከልምድ ጋር ቀስ በቀስ መምጣት አለበት።
► አንድ ሰው በስልጣን ላይ በፍጥነት ከተቀመጠ ምን ጉዳት ያመጣል?
(12) መልካም ስም ያለው
አንድ ሰው ፓስተር ሆኖ ከመሾሙ በፊት ከቤተክርስቲያን ውጭ ባሉ ሰዎች ዘንድ መልካም ስም ሊኖረው ይገባል። እሱ በሚያደርገው ሁሉ ታማኝ መሆኑን ማወቅ አለባቸው። ከመቀየሩ በፊት መጥፎ ስም ነበረው ከተባለ ፓስተር ከመሆኑ በፊት የተሻለ ስም ለመመስረት ጊዜ ያስፈልገዋል።
በአፍሪካ ያለ አንድ ፓስተር የእሁድ ጠዋት ስብከቱን ከሰበከ በኋላ ወደ ቤት ለመሄድ በአውቶብስ ተሳፈረ። ታሪፉን ከከፈሉ በኋላ ተቆጣጣሪው በጣም ብዙ ገንዘብ እንደመለሰ አስተዋለ። ታማኝ ሰው ስለነበር ተጨማሪውን ለውጥ “ይቅርታ ጌታዬ ባጋጣሚ ብዙ ገንዘብ ሰጥተኸኛል” በማለት ገንዘብን መልሶ ሰጠው። ተቆጣጣሪው እንዲህ ሲል መለሰ፦ “አይ በአጋጣሚ አላደረግኩትም። ከቤተክርስቲያንህ ውጭ ቆሜ ነበር እና ስለ ታማኝነት ስብከትህን ሰማሁ። እንደምትኖረውም ለማረጋገጥ ወስኜ ይህን አደረኩ” አለ። መጽሐፍ ቅዱስ መልካም ስም የአንድ ሰው ትልቁ ሀብት እንደሆነ ይናገራል (ምሳሌ 22፥1)። ስምህ ሲነሳ በሌሎች አእምሮ ውስጥ ምን ይመጣል?
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ቲቶ 1፥5-11 ያንብብ።
በቲቶ ውስጥ የተዘረዘሩት አብዛኛዎቹ የፖስተርነት መመዘኛዎች በ1ኛ ጢሞቴዎስ ባለው ምንባብ ውስጥም ተዘርዝረዋል።
► በቲቶ ውስጥ ባለው ምንባብ ውስጥ ምን ተጨማሪ የፓስተር ባህሪያት አሉ?
(13) ንቁ
ምንባቡ የአንድ ፓስተር ለሐሰት ትምህርት ምላሽ የመስጠት ችሎታን ያጎላል። ፓስተር በጎቹን ከሚጠብቅ እረኛ ጋር ሊመሳሰል ይችላል። እርሱ የጉባኤው ጠባቂ ነው። ከሐሰት አስተምህሮዎች እና ከተሳሳቱ ተጽዕኖዎች መጠንቀቅ አለበት። ፖስተሩ ህዝብን በትምህርታቸው የተጠበቁ እንዲሆኑ ማስተማር አለበት። ስለ መንፈሳዊ አደጋ ግለሰቦችን ለማስጠንቀቅ ዝግጁ መሆን አለበት። በቤተክርስቲያን ውስጥ ጎጂ የሆኑ ትምህርቶች እንዲሰጡ መፍቀድ የለበትም።
ፓስተሩ በእውነተኛ ትምህርት በደንብ የሰለጠነ እና አሳማኝ በሆነ መንገድ ማስረዳት የሚችል መሆን አለበት። ዓላማው በሐሰት ትምህርት ውስጥ ያሉትን ለማረም ነው ነገር ግን ከሁሉም በላይ ጉባኤው ወደ ስህተት እንዳይመራ መጠበቅ ነው። ፓስተሩ ያለማቋረጥ በእውቀቱ ላይ በጥናት መጨመር አለበት።
[1]
“ከኃጢያት በቀር ምንም የማይፈሩ
እና ከእግዚአብሔር በቀር ምንም የማይመኙ
መቶ ሰባኪዎችን ስጠኝ…
እነርሱ ብቻ የገሃነምን ደጆች ያንቀጠቅጡና
የሰማይ መንግስትን በምድር ላይ ያቆማሉ።”
- John Wesley
Previous
Next