የአገልግሎት አመራር
የአገልግሎት አመራር

Search Course

Type at least 3 characters to search

Search through all lessons and sections in this course

Searching...

No results found

No matches for ""

Try different keywords or check your spelling

results found

Lesson 17: ግላዊ ጉዳዮች፦ ገንዘብ፣ ጊዜ እና አለባበስ

1 min read

by Stephen Gibson


የገንዘብ አስተዳደር

የተጠያቂነት መርህ

► አንድ ተማሪ ለብድኑ ማቴዎስ 25፥14-30ን ያንብብ። ይህ ክፍል ስለ ገንዘብ አያያዝ ምን ይነግረናል?

ገንዘብ ለአገልግሎት ጠቃሚ ግብአት ነው። መሪዎች ጥሩ ውጤት በሚያስገኝ መንገድ ገንዘብን ማስተዳደር አለባቸው። እንድናስተዳድርበት ለሰጠን ሀብት ለእግዚአብሔር መልስ እንሰጣለን።

ጉዳት የደረሰበትን መንገደኛ የረዳውን የሳምራዊውን ታሪክ አስታውስ (ሉቃስ 10፥30-35)? የታሪኩ አላማ የሚያጋጥሟቸውን ሰዎች መውደድ ምን ማለት እንደሆነ ለማሳየት ነበር። ሆኖም ይህ ነጥብ የግድ በጸሐፊው የታሰበ ባይሆንም የተወሰኑ ዝርዝሮችን በመመልከት ሌላ ነጥብ ልንጠቅስ እንችላለን።

ሳምራዊው አህያ ነበረው እናም ለሰውየው እንክብካቤ የሚከፍለው ገንዘብ ነበረው። የተጎዳውን ሰው ከማግኘቱ በፊት ሀብቱን ቢያጠፋስ? እርሱን ለመርዳት አቅሙ አናሳ ይሆን ነበር። ለሌሎች ስቃይ እና የስብከተ ወንጌል አስፈላጊነት እናዝናለን የሚሉ ነገር ግን ለፍላጎታቸው ምላሽ እንዲሰጡ ሀብታቸውን ማስተዳደር ያቃታቸው ብዙ ሰዎች አሉ። ሌሎችን መርዳት በፍጹም አይችሉም።

ገንዘብ ለሚበላው እና ለሚጠፋው ነገር ሊወጣ ይችላል ወይም በዚህ ዓለም እና በዘለአለም ውስጥ ዘላቂ ዋጋ ላለው ነገር ሊወጣ ይችላል። ለፍላጎታችን ገንዘብ ማውጣት አስፈላጊ ነው ነገር ግን በተቻለ መጠን ለወደፊቱ ኢንቨስት ማድረግ አለብን።

ብዙ ሰዎች በቂ የለኝም ብለው ስለሚያስቡ ኢንቨስት አያደረጉም። ነገር ግን አንድ ሰው ትንሽ መደበኛ መጠን ቢቆጥብ እና ኢንቨስት ቢያደርግ ውሎ አድሮ ትልቅ ውጤት ይኖረዋል። ገበሬ ምንም ያህል ድሃ ቢሆንም እንደገና ለመትከል በቂ መቆጠብ እንዳለበት ይገነዘባል። ሀብታችንን ለመቆጠብ እና ለማፍሰስ መንገዶችን መፈለግ አለብን።

► አነስተኛ መጠን ለመቆጠብ እና ኢንቬስት ለማድረግ አንዳንድ መንገዶች ምንድናቸው?

የእምነት መርህ

ሐዋርያው ጳውሎስ በፊልጵስዩስ ላለች ቤተክርስቲያን ታላቅ ተስፋ ሰጠ። አገልግሎቱን ለመደገፍ መስዋዕትነት ከፍለዋል። እግዚአብሔር ፍላጎታቸውን እንደሚያሟላላቸው ቃል ገባላቸው (ፊልጵስዩስ 4፥19)።

ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ በጭንቀት ውስጥ መኖር እንደሌለባቸው ነገር ግን እግዚአብሔርን እንደሚሰጣቸው እንዲያምኑ ነገራቸው (ማቴዎስ 6፥25-34)። ከመሠረታዊ ፍላጎታቸው በፊት እንኳን ለእግዚአብሔር መንግሥት ቅድሚያ ሊሰጡ ይገባል።

እምነት ማለት እራሳችንን እና በእኛ ላይ ጥገኛ የሆኑትን ሰዎች ለማቅረብ ሃላፊነት አንወስድም ማለት አይደለም። ለፍላጎቶች ለማቅረብ እንድንችል መሥራት አለብን (ኤፌሶን 4፥28)። አንድ ሰው ለቤተሰቡ የሚያስፈልገውን ነገር ካላሟላ የአማኝ ምሳሌ አይደለም (1ኛ ጢሞቴዎስ 5፥8)።

ሰው በፍፁም ዝም ብሎ ተቀምጦ እግዚአብሄርን እንዲሰጠው መጠበቅ የለበትም። እግዚአብሔር በሥራና ጠቃሚ ነገር በማፍራት እንድንጠቅም ነድፏል።

እምነት ማለት ያለ እግዚአብሔር በረከት መኖር እንደማንችል እንገነዘባለን ማለት ነው። የእኛ ጥንካሬ እና የመሥራት እድላችን ከእግዚአብሔር ነው እና ከሥራችን ባልሆኑ ነገሮች ይባርካል። በእግዚአብሔር ስለምንደገፍ ኢየሱስ እንዳዘዘው “የዕለት እንጀራችንን ዛሬ ስጠን” (ማቴዎስ 6፥11) ብለን መጸለይ አለብን።

ለሌሎች ለጋስ መሆን አለብን ምክንያቱም

  • እግዚአብሔር እንደሚሰጠን እናውቃለን።

  • ስራችን ያለንን ሁሉ አያፈራም።

  • የእግዚአብሔር በረከት አይገባንም።

  • በመስጠት የእግዚአብሔርን ፍቅር እናሳያለን።

ሌሎች እንደማይጠግቡ እያወቀ ብዙ ምግብ እንደሚወስድ ራስ ወዳድ ሰው መሆን የለብንም። እግዚአብሔር ብዙ ነገር አለው እና ከዚህ በላይ እንደማይሰጠን ስግብግብ ወይም ድብቅ እንድንሆን አይፈልግም።

የአገልግሎት መሪ የራሱን ገንዘብ ብቻ ሳይሆን የአገልግሎት ሃብትን ያስተዳድራል። እግዚአብሔር ፈቃዱን ለሚከተል አገልግሎት ይሰጣል። ይሁን እንጂ ፈቃዱ ሁልጊዜ ለእኛ ግልጽ ሆኖ የሚታይ አይደለም። አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ተቋምን በመጠበቅ ላይ ያተኩራሉ እና ከእግዚአብሔር ግልጽ መመሪያ መፈለግን ቸል ይላሉ። አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ጥሩ ነገር ለማድረግ ይሞክራሉ። ነገር ግን እግዚአብሔር በሚፈልገው መንገድ አያደርጉትም። በእነዚህ ነገሮች ላይ ሁልጊዜ ፍጹም ማስተዋል አይኖረንም ነገር ግን ለአገልግሎት የሚሆን የገንዘብ እጥረት ስለ እግዚአብሔር ፈቃድ የተሻለ ግንዛቤ እንድንፈልግ ሊያነሳሳን ይገባል።

የሐቀኝነት መርህ

የእምነት መርህ ወደ ሐቀኝነት መርህ ይመራል። አምላክን የሚያሳዝን ነገር ማድረግ የለብንም ምክንያቱም ስለምናከብረውና በእርሱ መባረክ ስለምንፈልግ ነው።

በአምላክ ላይ ከታመንክና በእርሱ ላይ እምነት ካለህ ሐቀኝነት የጎደለው ነገር በማድረግ የምታገኛቸውን አጋጣሚዎች ትቃወማለህ። አንድ አጋጣሚ ሲመጣ “እግዚአብሔር በዚህ መንገድ ያቀርባል?” የሚለውን ጥያቄ ግምት ውስጥ ማስገባት አለብህ። ዕድሉ ሐቀኝነት የጎደለው በመሆን አንድን ነገር ለማግኘት ከሆነ እግዚአብሔር በሚያቀርበው መንገድ እንዳልሆነ እናውቃለን። ለጥቅም ሲል ስህተት የሚሰራ ሰው ለፍላጎቱ በእግዚአብሄር አይታመንም።

በአገልግሎት ላይ ያለ ሰው አብዛኛውን ጊዜ የራሱ ያልሆኑ ሀብቶችን ያስተዳድራል። የአገልግሎት ገንዘብን ከራሱ ገንዘብ መለየት ለእርሱ አስፈላጊ ነው። በአንዳንድ ባሕሎች ሰዎች ይህን ደንብ በቀላሉ አይረዱትም። ነገር ግን በአገልግሎት፣ በመንግሥትም ሆነ በንግድ ሥራ፣ ሰዎች ይህን ልዩነት ማድረግ ይችላል ብለው ካላሰቡ በቀር የሥልጣን ቦታ አይሰጠውም። አንድ ሰው የተቋሙን ገንዘብ እንደራሱ ከተጠቀመ እምነት እየጣሰ ነው (1ኛ ቆሮንቶስ 4፥2)።

የአገልግሎት መሪ ከተቋሙ ገንዘብ ጋር ጥንቃቄ የተሞላበት ተጠያቂነትን የሚጠብቁ ፖሊሲዎችን ማቋቋም አለበት። ገንዘቡን ብቻውን መሰብሰብ እና ማስተዳደር የለበትም። ብዙ ሰዎች መዝገቦችን በመያዝ እና በማውጣት ላይ መሳተፍ አለባቸው።

የአገልግሎት ድጋፍ መርህ

እግዚአብሔር አገልግሎትን በገንዘብ መደገፍ እንዳለበት ነድፏል። ሆኖም የአገልግሎት መሪው ብዙ ጊዜ አገልግሎቱ ሙሉ በሙሉ ድጋፍ በያገኝበት ሁኔታ ውስጥ ይሆናል።

ለአንድ ክርስቲያን መሪ ገንዘብ የመሪነት ቦታን የሚቀበልበት ምክንያት ወይም የተቻለውን ሁሉ ጥረት የሚያደርግበት ምክንያት ሊሆን አይገባም። ለአገልግሎት የሚያነሳሱት ምክንያቶች እግዚአብሔርን የመታዘዝ ግዴታ፣ እግዚአብሔርን ደስ የማሰኘት ፍላጎት እና ሰዎች እንዲገለገሉ ባለው ፍቅር ነው (1ኛ ጴጥሮስ 5፥2፣ 1ኛ ቆሮንቶስ 9፥16፣ ዮሐንስ 21፥15-17)።

ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን እንዲያገለግሉ በላካቸው ጊዜ “በነጻ የተቀበላችሁትንም በነጻ ስጡ” (ማቴዎስ 10፥8) አለ። በአገልግሎት ላይ ዋጋ ማውጣቱ ስህተት ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ካሉት በጣም ጠንካራ ተግሣጾች አንዱ መንፈሳዊ ኃይልን በመክፈል ትርፍን ለራሱ ለሚያቀርብ ሰው ተሰጥቷል (ሐዋርያት ሥራ 8፥18-23)።

[1]አገልግሎት እንደሌሎች የሥራ ዓይነቶች ገንዘብን አያመርትም ምክንያቱም የሚሸጥ ምርትና አገልግሎትን አይሰጥም። አገልግሎት የሚደገፈው ሌላ ሙያ ያላቸው ሰዎች መደገፍ እንዳለባቸው ሲወስኑ ብቻ ነው።

የአገልግሎት መሪ የአገልግሎቱን ጥቅም እና ለአገልግሎቱ ያለውን ቁርጠኝነት በመናገር ሰዎች እንዲደግፉ ማበረታታት ይችላል። አብዛኛውን ጊዜ አገልግሎት ከመጀመሩ በፊት ድጋፍ ለማግኘት መጠበቅ አይችልም። የአገልግሎቱ ዘገባዎች ቋሚ፣ ተጨባጭ እና ሙሉ በሙሉ ሐቀኛ መሆን አለባቸው።

ብዙውን ጊዜ ሰዎች ደጋፊ የሚሆኑበት ምክንያት የአገልግሎቱን ጥቅም ስላዩ እንጂ አገልግሎቱ ድጋፍ ስለሚያስፈልገው አይደለም። የአገልግሎት መሪ ስለ ፍላጎቱ በማውራት ድጋፍ ለማሰባሰብ መሞከር ሳይሆን የአገልግሎቱን ውጤት በማምጣትና የአገልግሎት ራዕዩን በማስረዳት ነው። እርሱ ከሚያገለግላቸው ሰዎች ጋር ያለውን ቁርጠኝነት እንዲያዩ እና ለእነርሱ የሚሰጠውን አገልግሎት እንዲያደንቁ ግንኙነቶችን መገንባት አስፈላጊ ነው።

አንዳንድ ሰዎች ለድርጅቱ ከመስጠት ይልቅ መሪውን በግል መደገፍ ይፈልጉ ይሆናል። መሪው ድርጅቱን ከመገንባት ይልቅ የራሱን ድጋፍ እንዳይገነባ መጠንቀቅ አለበት። ስራው ድርጅቱን መገንባት ነው።

መሪው ዕዳን ማስወገድ አለበት። ገንዘብ መበደር ከወደፊቱ ገንዘብ ማውጣት ነው። ዕዳ ወደፊት ውሳኔ ለማድረግ ነፃነትን ያስወግዳል። ዕዳ ማለት እርስዎ እዚያ ከመገኘትዎ በፊት ስለ ወደፊቱ ጊዜ ውሳኔ እያደረጉ ነው ማለት ነው። ዕዳው የወደፊቱን ሀብቶች እያጠፋ ሲሆን የወደፊቱ ፍላጎቶች አሁንም የማይታወቁ ናቸው።

መሪው ከግል ዕዳ መራቅ አለበት ምክንያቱም ወደፊት የአገልግሎት ውሳኔውን ስለሚገድበው ነው። መሪው ድርጅቱን ወደ ዕዳ ከመምራት መቆጠብ አለበት። እግዚአብሔር የሰጠውን ገንዘብ ብቻ ተጠቀም። አምላክ ዕዳውን የሚከፍልበትን መንገድ እንደሚሰጥ በማሰብ አትበደር። አምላክ ለአንድ የተወሰነ ፍላጎትን ማሟላት ከፈለገ፤ ከመበደርዎ በፊት ሊፈጽመው ይችላል ከዚያ በኋላ ሳይሆን። መበደር የእግዚአብሄርን ፈቃድ የማወቅ አንዱን መንገድ ያስወግዳል ምክንያቱም እግዚአብሔር የሚሰጠውን ለማየት አትጠብቅም ማለት ነው።

ትንታኔ

► በገንዘብ መርሆዎች ምክንያት ግቦችዎን ወይም ድርጊቶችዎን እንዴት እንደሚቀይሩ ይጠብቃሉ?


[1]“በእግዚአብሔር መንገድ የተሠራው የእግዚአብሔር ሥራ የእግዚአብሔርን አቅርቦት አያጣም።”

- J. Hudson Taylor