Search Course
Search through all lessons and sections in this course
Searching...
No results found
No matches for ""
Try different keywords or check your spelling
ክርስቲያናዊ እምነት
Course Description
ይህ ትምህርት መሰረታዊ የሆኖ በክርስትና ስነመለኮት ምድብ ውስጥ እንደ እግዚአብሔር፥ ክርስቶስ፥ ሀጥያት ፥ ድነት እና ሌሎች ዋና አስተምሮዎችን ያስረዳል። ተማሪዎች በአስተምሮ ላይ ያሉ ስዕተቶችን ማስወገድን ይማራሉ። ተማሪዎቸ ሌሎችን ስለ ክርስቲያናዊ አስተምሮ ሌሎችን ለማስተማር ብቁ ይሆናሉ።
What You'll Learn
Course Objectives
(1) የክርስትና እምነት መሰረታዊ አስተምሮዎችን መማር
(2) መጽሐፍ ቅዱስን በሚገባ እንደ አስተምሮ ምንጭ እና ባለስልጣን በሚገባ ይጠቀማሉ
(3) በአስተምሮ ውስጥ ያሉ ዋና ዋና ስዕተቶችን ያለያሉ
(4) ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸውን ግንኙነት ለማጣናከር የሚረዳ መረዳትን ይገበያሉ
(5) ሌሎችን ለማስተማር የሚረዳ ይዘት እና ቅርፅ ያገኛሉ
Introduction
ለክፍል መሪዎች የሚሆን መምሪያ
እያንዳንዱ ትምህርት 90 ደቂቃ እንደሚወስድ እንገምታለን። ትምህርቶቹ በሁለት ክፍለ ግዜ ለቡድኑ መስጠት የተሻለ ነው። ቡድኑ ሁለት ግዜ ቢገናኝ፥ አንዳንድ መምሪዎች ሊስተካከሉ ይገባል። ለምሳሌ ሁለቱም ግዜ ፈተና መሰጠት የለበትም።
እያንዳንዱ ተማሪ ይህ መጽሐፍ በእጁ ላይ ሊኖር ይገባል።
ለክፍል መሪዎች የሚሆኑ ማስታወሻዎች ስለ ትምህርቶቹ የተወሰኑ ክፍሎች መመሪያዎችን በመያዝ በመላው ኮርሱ ውስጥ ተካተዋል።. እነሱ በኢታሊክ ተጻፈዋል።
በከፍለ ግዜው መጀመርያ ላይ - ያለፈውን ትምህርት መሰረት ፈተና ስጡ። እያንዳንዱ ተማሪ ያለምንም እርዳታ ፈተናውን መመለስ ያለበት የተማረውን በማስታወስ መሆን አለበት። ተማሪው ፈተናውን ማለፍ ካልቻለ፥ ሌላ ግዜ እንዲፈተን ዕድል መስጠት (በግምት የሚሰጥ ግዜ - 10 ደቂቃ)። የፈተና መልስ ቁልፍ ከ ShepherdsGlobal.org ማውረድ ይቻላል።
ከፈተናው በሓላ፥ ካለፈው ትምህርት አላማ ዝርዝር እንደ ማጥኛ ጥያቄዎች ተጠቀሙ። ከእያንዳንዱ አላማ ጥያቄ ተማሪዎችን በመጠየቅ ተማሪዎች እንዲያስረዱ ፍቀዱ (በግምት የሚሰጥ ግዜ ፤ 15 ደቂቃ)።
አዲስ ትምህርት የተሰጠውን ክፍል በማንበብ ጀመሩ፤ ተማሪዎችም ስለ ትምህርቱ ይዘት ክፍሉ የሚናገረውን እንዲወያዩ አድርጉ (በግምት የሚሰጥ ግዜ- 10 ደቂቃ)
ትምህርቱ ማስተማርያ መፀሐፍ ውስጥ እያንዳንዱን ክፍል በማንበብ እና በማስረዳት ተመልከቱ። የክፍሉ አባላት አንዳንድ ዘርፎችን ማስተማር ይችላሉ ( በግምት የሚሰጥ ግዜ- 45 ደቂቃ)
በዚህ ትምህርት ውስጥ ብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ዘርፎች ጥቅም ላይ ውለዋል። የመጽሐፍ ቅዱስ ዘርፎች ማጣቀሻ በቅንፍ ውስጥ አንብብ ከሚለው ጋር ያሉት በክፍል ውስጥ ጮክ ተብሎ መነበብ አለበት። ሌሎች የመጽሐፍ ቅዱስ ዘርፎች ግን በማስተማርያው መጽሐፍ ውስጥ ያለውን ላለው ሃሳብ ድጋርፍ ሚሰጡ ናቸው። ሁል ግዜ በክፍል ውስጥ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎቸን መመልከት እና ማንበብ አስፈላጊ አይደለም።
የውይይት ጥያቄዎች እና የክፍል ውስጥ እንቅስቃሴዎች ► በዚህ ምልክት ይለያሉ። አንዳዴ የውይይት ጥያቄዎች የትምህርቱን ክፍል ያስተዋውቃሉ፤ ሌላ ግዜ በክፍል ውስጥ የነበረውን ትምህርት ይከልሳሉ። የክፍሉ መሪ ጥያቄዎችን መጠየቅ አለበት እና ለተማሪዎችም መልሱ ላይ እንዲወያዩ ግዜ መስጠት አለበት። በዚህ ግዜ መልሱን ሙሉ ለሙሉ ማስረዳት አስፈላጊ አይደለም፥ በተለይ ጥያቄው ለክፍለ ግዜው መግቢያ ከሆነ።
በክፍለ ግዜው መጨረሻ ላይ ሙሉ ክፍሉ አብሮ ሁለት ጊዜ ‘የእምነት መግለጫውን’ ያንብብ።
በእያንዳንዱ ትምህርት መጨረሻ ላይ- እያንዳንዱ ተማሪ ከተዘረዘሩት መካከል አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይመደባል። ከሚቀጥለውን ክፍለ ግዜ በፊት፤ ክፍሉን አንብቦ እና አንድ አንቀፅ ክፍሉ ስለ ትምህርቱ ርዕሰ ጉዳይ ስለሚናገረው ይፃፍ። የፃፉትንም አንቀፅ ለክፍሉ መሪ በሚቀጥለው ክፍለ ግዜ ያሳዩ።
ቢያንስ ለሶስት ግዜ ተማሪው ይህንን ትምህርት ወይም የትምህርቱን አንድ ክፈል በክፍል ውስጥ ለሌሉ ሰዎች ያስተምር። ይህም በቤተክርስቲያን ውስጥ ላለ ክፍል፥ ለቤት ለቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ቡድን ወይም ሌላ ስብስብ ውስጥ መሆን ይችላል። በእያንዳንዱ ክፍለ ግዜ ማለቂያ ላይ ተማሪዎችን ስለ ቤት ስራ ማስታወስ እንዲሁም ካለፈው የትምህርት ግዜ በሓላ ያስተማሩት ቡድን ካለ ሪፖርት እንዲያደርጉ ጠይቁ።
በክፍለ ግዜው መጨረሻ ላይ ቀጣዩን ትምህርት ከሚቀጥለውን ክፍለ ግዜ በፊት አንብበው እንሚመጡ አስታውሷቸው (ለማሳሰቢያ እና ለቤት ስራ የሚያስፈልገው ግዜ በግምት - 10 ደቂቃ)
ተማሪዎች ክፍለ ግዜውን የመሳተፍ እና የቤት ስራቸውን በግዜ የመስራት ግዴታ አለባቸው። ተማሪ ክፍል ከቀረ፥ ያለፈውን ትምህርት ማጥናት፥ ፈተናውን መስራት እና የቤት ስራውን መፈፀም አለበት። በትምህርቱ መጨረሻ ላይ የተሰጡ እና የተጠናቀቁ የቤት ስራዎችን መመዝገቢያ ቅፅ አለ።
ለተማሪዎች መምሪያ
ለትምህርት ወደ ክፍል ከመምጣታችሁ በፊት በውይይቱ ላይ በተሻለ ግንዛቤ መሳተፍ እንድትችሉ የተሰጠውን መማርያ አንብባችሁ መምጣት አለባችሁ።
በእያንዳንዱ ክፍለ ግዜ መጀመርያ ላይ ያለፈውን ትምህርት መሰረት ፈተና ስለሚኖር በተሰጠው የማጥኛ ጥያቄዎች መሰረት ተዘጋጁ።
ወደ ክፍል ስትመጡ መጽሐፍ ቅዱስ፥ በታተመ የትምህርቱን ቅጂ እና የራሳችሁን ማስታወሻ መጨመር የሚያስችላችሁ እስኪብርቶ ይዛችሁ ወደ ክፍል መምጣት አለባችሁ።
የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎትን ለማጣቀስ፥ የውይይት ጥያቄዎችን ለመመለስ እና የክፍሉ መሪ በሚመራው መንገድ ለመሳተፍ ተዘጋጅታችሁ መምጣት አለባችሁ።
በእያንዳንዱ ትምህርት መጨረሻ ላይ አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይመደብላችሃል፤ ከሚቀጥለውን ክፍለ ግዜ በፊት ክፍሉን አንብባችሁ፤ በአንድ አንቀፅ ስለ ትምህርቱ ዋና ሃሳብ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሉ የሚለውን በማስቀመጥ፤ ለክፍሉ መሪ ማሳየት።
ትምህርቱ በሚሰጥበት ወቅት ቢያንስ ሶስት ግዜ የተማሩትን ትምህርት ወይምን የተመረጠ ክፍል በመውሰድ በክፍሉ ውስጥ ለሌሉ ሰዎች ማስተማር አለባቹ። ይህንም የማስተማር ሀላፊነት በቤተክርስቲያን ውስጥ ላለ ክፍል፥ የቤት ለቤት የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ቡድን ወይን በሌላ መንገድ ሊሆን ይችላል። ባስተማራችሁ ግዜ ሁሉ ለክፍል መሪያችሁ አስታውቁ።
Ready to Start Learning?
Choose a lesson to begin your journey through this course.
Christian Beliefs
15 lessons · አማርኛ
Print Course
Request Submitted!
Your print request has been recorded. Your download should begin shortly.
Download Print-Ready FileFree to print for ministry use. No changes to content, no profit sales.
SGC exists to equip rising Christian leaders around the world by providing free, high-quality theological resources. We gladly grant permission for you to print and distribute our courses under these simple guidelines:
- No Changes – Course content must not be altered in any way.
- No Profit Sales – Printed copies may not be sold for profit.
- Free Use for Ministry – Churches, schools, and other training ministries may freely print and distribute copies—even if they charge tuition.
- No Unauthorized Translations – Please contact us before translating any course into another language.
All materials remain the copyrighted property of Shepherds Global Classroom.
Questions? info@shepherdsglobal.org
Order Physical Course
ክርስቲያናዊ እምነት
Total
$21.99Added to Cart!
Download Course
By submitting your contact info, you agree to receive occasional email updates about this ministry.
Additional Files
Audio Course Downloads
ክርስቲያናዊ እምነት
Download audio files for offline listening
No audio files are available for this course yet.
Check back soon or visit our audio courses page.
Share This Course
ክርስቲያናዊ እምነት
Share this free course with others