የትምህርት ዓላማዎች
በዚህ ትምህርት መጨረሻ ተማሪው የሚከተሉትን ማድረግ ይኖርበታል፦
(1) ገንዘብን እና ሀብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም እና ለማስተዳደር የእግዚአብሔርን መርሆች ለመታዘዝ ቃል መስጠት።
(2) ስለ ገንዘብ ተገቢ ያልሆነ እምነት እና አጠቃቀም የሚያስከትለውን መንፈሳዊ አደጋዎች እና እነርሱን እንዴት ማስወገድ እንደሚቻል መረዳት።
Lesson
Playlist
Search through all lessons and sections in this course
Searching...
No results found
No matches for ""
Try different keywords or check your spelling
1 min read
by Stephen Gibson
በዚህ ትምህርት መጨረሻ ተማሪው የሚከተሉትን ማድረግ ይኖርበታል፦
(1) ገንዘብን እና ሀብቶችን በአግባቡ ለመጠቀም እና ለማስተዳደር የእግዚአብሔርን መርሆች ለመታዘዝ ቃል መስጠት።
(2) ስለ ገንዘብ ተገቢ ያልሆነ እምነት እና አጠቃቀም የሚያስከትለውን መንፈሳዊ አደጋዎች እና እነርሱን እንዴት ማስወገድ እንደሚቻል መረዳት።
John Wesley በእንግሊዝ ከ1703-1791 ኖረ። በአብያተ ክርስቲያናት ዘንድ ተቀባይነት ለማያገኙ ድሆች በውጭ አካባቢ ወንጌልን ሰበከ። ገንዘቡን ጨምሮ በእያንዳንዱ የሕይወት ዝርዝር ውስጥ እግዚአብሔርን ለማክበር በመፈለግ በጥንቃቄ ኖረ። አማኞች ገንዘብ ሲያገኙ የሚቻላቸውን ሁሉ እንዲቆጥብ እና የሚችሉትን ሁሉ እንዲሰጡ አስተምሯል። በሥነ-ምግባር የታነፁ የገንዘብ ልማዶችን የመጠቀም ታማኝ ምሳሌ ነበር። የሚሰጠው ብዙ ገንዘብ ይኖረው ዘንድ አመታዊ ወጪውን ቀነሰ። ከዚያም ገቢው ሲጨምር ወጭውን በመቆጣጠሩ እና የሚቀረውን ሰጥቷል። በህይወት ዘመኑ ብዙ ሀብት ቢያገኝም ሲሞት በእጁ የነበረው ጥቂት ሳንቲሞች ብቻ ነበሩ። Wesley እግዚአብሔር ሰዎች የእርሱን ገንዘብ እንዲያስተዳድሩ እንደሚተማመን ያውቅ ነበር እናም አማኞች ከገንዘብ ጋር በተያያዘ የእግዚአብሄርን መርሆች መከተል እንዳለባቸው አስተምሯል።
አዲስ ኪዳን ገንዘብን ከሌሎቹ ጉዳዮች በላይ የሚጠቅሰው ገንዘብ ለእግዚአብሔር በጣም አስፈላጊ ስለሆነ ሳይሆን ሰዎች በገንዘብ ላይ ብዙ ችግር ስላለባቸው ነው።
ፈጣሪ እንደመሆኑ እግዚአብሔር የሰዎችና የሀብታቸው ሁሉ ባለቤት ነው። አማኞች እንደመሆናችን መጠን የእግዚአብሔር ነን እርሱ በተለየ መንገድ ዋጅቶናልና። ራሳችንን ለእግዚአብሔር ክብር መዋል ያለባቸውን የንብረት አስተዳዳሪዎች አድርገን መቁጠር አለብን።
በመልካም ነገሮች መዝናናት ስህተት አይደለም። ሁሉንም ነገር በማመስገን እና በትህትና ከተቀበልን እግዚአብሔር ሊባርከን ደስ ይለዋል።
ነገር ግን ገንዘብ ለብዙ ሰዎች መንፈሳዊ አደጋ ነው።
► ሀብታም መሆን ማለት ምን ማለት ነው?
አንድ ሰው እንደ ሀብታም ሊቆጠር የሚችልባቸው የተለያዩ ምክንያቶች አሉ።
ከመሠረታዊ ፍላጎቶችዎ በላይ ለመግዛት ገንዘብ ካለዎት በዓለም ላይ ካሉት ቢያንስ ከግማሽ በላይ ሰዎች የተሻለ ሀብታም ነዎት። ብዙ ሰዎች በዚያ ቀን ለሚመገቡት ምግብ በየቀኑ ይሠራሉ፤ ሥራቸውን የሚከለክል ነገር ቢፈጠር የሚበሉት ምግብ አይኖራቸውም።
ብዙውን ጊዜ ሰዎች በራሳቸው ማህበረሰብ ውስጥ ካሉት አብዛኛዎቹ ሰዎች የበለጠ ሀብት ያለውን ሰው ሀብታም አድርገው ይመለከቱታል። አኗኗሩ ከብዙ ሰዎች የበለጠ ገንዘብ እንደሚያጠፋ ያሳያል። ሰዎች ከፍ ካለ ማህበራዊ መደብ እንደሆነ አድርገው ይመለከቱታል። ብዙ ሰዎች ሊገዙ በማይችሉት የቅንጦት ዕቃዎች መደሰት ይችላል። በሥልጣን ላይ ካሉ ሰዎች ጋር ተፅዕኖአዊ ግንኙነት አለው። በሀብቱ ምክንያት ሰዎች እርሱን ለማገልገል ዝግጁ ናቸው።
መጽሐፍ ቅዱስ ለሀብታሞች ልዩ መመሪያዎች እና ማስጠንቀቂያዎች አሉት።
በጣም ከባዱ ማስጠንቀቂያ ኢየሱስ ሀብታም ሰው ወደ መንግሥተ ሰማያት መግባቱ በጣም አስቸጋሪ እንደሆነ የተናገረው ሐሳብ ነው (ማቴዎስ 19፥24)።
ሐዋርያው ጳውሎስ ለሀብታሞች ከተናገረው መልእክት ስለሀብት አደገኛነት የተወሰነ ግንዛቤ ማግኘት እንችላለን።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥17-19ን ያንብብ።
ጳውሎስ ሀብታሞች ራሳቸውን ከሌሎች ሰዎች የላቀ ደረጃ አድርገው እንዳይቆጥሩ ያስጠነቅቃል። ሀብታም ሰዎች ራሳቸውን ከሌሎች በተሻለ እንዲያስቡ ይፈተናሉ። ያዕቆብ ቤተክርስቲያን ሰዎችን በሀብታቸው ወይም በማኅበራዊ ደረጃቸው ምክንያት በማክበር ተመሳሳይ ስህተት እንዳትሠራ ያስጠነቅቃል (ያዕቆብ 2፥1-4)።
ባለጠጋ በሀብቱ ምክንያት መረጋጋት አይገባውም ነገር ግን በእግዚአብሔር ላይ መደገፍ አለበት። አንድ ሀብታም ሰው የገንዘብ አቅም ሲይዝ የእግዚአብሔር አቅርቦት እንደሚያስፈልገው እንዲሰማው ማድረግ ከባድ ነው። የእግዚአብሔር እርዳታ እንደሚያስፈልግ ባለመሰማት በመንፈሳዊ ግድ የለሽ ለመሆን መፈተን አለ (ዘዳግም 8፥6-18)።
ባለጠጎች ለጋስ ሰጪዎች መሆን እና በገንዘባቸው መልካም ነገሮችን ማከናወን አለባቸው።
በያዕቆብ 5፥5 ላይ ካሉት ዓለማዊ ባለጠጎች ኩነኔ አንዱ ሌሎች ሲሰቃዩ እነርሱ በተድላ መኖራቸው ነው። በጥበብ በመስጠት ብዙ መልካም ነገር ሊከናወን ይችላል። ገንዘብ ደስታን ሊገዛ አይችልም ነገር ግን ብዙ መከራን ያስወግዳል። አንድ ሰው በቅንጦት እየኖረ የሌላውን ስቃይ ችላ ማለቱ ስህተት ነው።
በነቢዩ አሞጽ በኩል እግዚአብሔር ስለ ሰው ልጆች ፍትህ (ለድሆችና ለተጨቆኑ ምሕረትና ርኅራኄን) በእነዚህ ቃላት የልብ ሀሳብን ገልጿል “ነገር ግን ፍትሕ እንደ ወንዝ፣ ጽድቅም እንደማይደርቅ ምንጭ ይፍሰስ” (አሞጽ 5፥24)። ብልጽግና ወደ ምቾት፣ ራስን ማስደሰት እና ለድሆች ችግር ግድየለሽነት ሲመራ እግዚአብሔር በብልጽግና ላይ ፍርድን ተናገረ (አሞጽ 6፥1፣ 3-6፤ አሞጽ 8፥4-7፣ 11-12)።
እያንዳንዱ አማኝ ድሆችን እና የተጨቆኑትን ለመርዳት በመስዋዕትነት መስጠት፣ ለሀገር ውስጥ ቤተክርስቲያኑ አሥራት መስጠት እና ለወንጌል መስፋፋት የሚስዮናዊነት ሥራ መደገፍ አለበት። John Wesley በዘመኑ የነበረችው ቤተ ክርስቲያን በዓለም ላይ ብዙም ተጽዕኖ ያላሳደረችበት ሦስት ምክንያቶች እንዳሉ ተናግሯል፦
1. የጤናማ አስተምህሮ አለመኖር
2. ተጠያቂነት ያለው ስነ ምግባር አለመኖር
3. የግል መስዋዕትነት ማጣት
► አንድ ተማሪ ለብድኑ 1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥8-10ን ያንብብ።
ስለ ገንዘብ የሚሰጠው ማስጠንቀቂያ ለሀብታሞች ብቻ የተሰጠ አይደለም። ብዙ ድሆች ደሀ ስለሆኑ ፈጽሞ ደስተኛ ሊሆኑ እንደማይችሉ ይሰማቸዋል። ገንዘብን መውደድ ክፋትን ሁሉ እንደሚያመጣ መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል። ይህ ማስጠንቀቂያ ለሁሉም ሰው ይሠራል።
የገንዘብ ፍቅር ፈጽሞ ሊጠገብ አይችልም። ገንዘብን የሚወድ ሰው በምንም ያህል የገንዘብ መጠን አይጠግብም (መክብብ 5፥10)። መጽሐፍ ቅዱስ ገንዘብን ከመውደድ እንድንርቅና በመሠረታዊ ፍላጎታችን እንድንረካ ይነግረናል (ዕብራውያን 13፥5)።
ሀብታም ለመሆን በጉጉት የሚፈልግ ሰው ለባህሪው ለመገዛት ብዙ ፈተናዎች አሉት። ሀብታም ለመሆን በሚሞክርበት ሂደት አንድ ሰው እምነቱን ትቶ ከሚጠብቀው ደስታ ይልቅ ብዙ ሀዘኖችን ሊያገኝ ይችላል።
አንዳንድ ጊዜ የሀይማኖት መሪዎች ሀብት ለመስጠት ቃል በመግባት ተከታዮችን ይስባሉ። እምነት ያለው ሰው ሀብት ሊኖረው ይገባል ይላሉ። በድሃ ማህበረሰቦች ውስጥ ያሉ ብዙ ሰዎች በእነዚህ ተስፋዎች ይሳባሉ ምክንያቱም ህይወታቸው አስቸጋሪ ስለሆነ ነው። እነዚህ መሪዎች ስለ ገንዘብ ያለማቋረጥ ይነጋገራሉ እና ይሰብካሉ እናም በዓለም ላይ ያሉ ሰዎች የሚያሳዩትን የገንዘብ ስኬት ምልክቶች ማሳየት በመቻላቸው ኩራት ይሰማቸዋል።
መጽሃፍ ቅዱስ እርካታ ያለው እግዚአብሔርን መምሰል ትልቅ ዋጋ እንዳለው ይናገራል (1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥6)። በሃይማኖታዊ መንገድ ሃብትን የሚያሳድድ ሰው እንደማንኛውም ሀብትን እንደሚያሳድድ የአለም ሰው አደጋ አለው። ለሀብት ቃል የሚገቡ አብያተ ክርስቲያናት ወደ ግል ፍላጎታቸው በመማረክ ያልተለወጡ ሰዎችን ይስባሉ። ሆኖም እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት የተስፋውን ቃል ፈጽሞ ባልተቀበሉ እና በተስፋ በሚጠባበቁ ሰዎች ተሞልተዋል። በሀብት ወንጌል አስተምህሮ ሀብታም የሆኑት ብቸኛ ሰዎች ከሚያምኑአቸው ሰዎች መባ የሚሰበስቡ ሰባኪዎች ብቻ ናቸው።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ፊልጵስዩስ 4፥10-13 ያንብብ።
የፊልጵስዩስ አማኞች ለእርሱ ድጋፍ መስዋዕት ስለላኩ ጳውሎስ አመሰገነ። በማንኛውም ሁኔታ በረሃብም ቢሆን መርካትን እንደተማረ ነገራቸው። ይህ አባባል የሚያሳየን ጳውሎስ ሁልጊዜ የተትረፈረፈ ገንዘብ እንዳልነበረው ነው። በእግዚአብሔር እርዳታ ሁሉንም ነገር ማድረግ እንደሚችል ተናግሯል። የዚያ ዓረፍተ ነገር አውድ የሚያሳየው በማናቸውም ሁኔታ እርካታን እና ለእግዚአብሔር ታማኝ መሆንን ማለቱ ነው።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ምሳሌ 11፥1ን ያንብብ።
ይህ ጥቅስ የሚያወራው አንድን ነገር በክብደት ለመሸጥ ስለሚውሉ እንደ ፍራፍሬ ወይም አትክልት ወይም ስጋ ላሉ ሚዛኖች ነው። አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ተጨማሪ ገንዘብ ለመውሰድ የሀሰት ክብደትን ለመስጠት የተነደፉ ሚዛኖች አሏቸው። ይህ ጥቅስ እግዚአብሔር አለመታመንን ይጠላል ይላል።
ብዙ ሰዎች ለገንዘብ ሲሉ ታማኝነት የጎደለውን ነገሮች ያደርጋሉ። በዚህ ኮርስ የሚቀጥለው ትምህርት ስለ ታማኝነት ጉዳይ ነው።
ሐዋርያው ጳውሎስ ለፊልጵስዩስ አማኞች ጻፈ እና እግዚአብሔር የሚያስፈልጋቸውን እንደሚሰጣቸው ቃል ገባላቸው። ይህ ድንቅ ቃል ኪዳን ነው። የነበረውን ሁኔታ ለማየት የተጠቀሰበትን ምንባብ መመልከት አለብን።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ፊልጵስዩስ 4፥15-19 ያንብብ።
ቤተክርስቲያን ለጳውሎስ የገንዘብ ድጋፍ ላከች። እርሱም ለእግዚአብሔር መስዋዕት ነው አለ። እግዚአብሔር ፍላጎታቸውን እንደሚያሟላላቸው ቃል ገባላቸው። ለገንዘባቸው ታላቅ መባዛት እንደሚሆን ቃል አልገባም።
ይህ ቃል ኪዳን ኃላፊነት ለጎደላቸው ወይም አባካኝ ለሆኑ ሰዎች አልነበረም። በመንፈሳዊ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ነገሮች መሠረት ገንዘባቸውን ለሚያስተዳድሩ ሰዎች ነበር።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ማቴዎስ 6፥25-33 ያንብብ።
ኢየሱስ እግዚአብሔር ወፎችን እንዴት እንደሚመግብ እና አበቦችን እንደሚያስጌጥ ተናግሯል እናም እኛን እንደሚንከባከበን ቃል ገባ። ስለ ሕልውናችን እንዳንጨነቅ ይነግረናል። የእግዚአብሔርን መንግሥት ካስቀደምን ፍላጎታችን እንደሚሟላልን ቃል ገብቷል።
ሰዎች ስለወደፊቱ እንጂ ስለ ዛሬ አይጨነቁም። እግዚአብሔር ለረጅም ጊዜ ሁሉንም ነገር አስቀድሞ ለመስጠት ቃል አልገባም። በብሉይ ኪዳን መና በወደቀ ጊዜ በየቀኑ ይመጣ እንደነበር አስታውሱ (ዘፀአት 16)። በተመሳሳይም ኢየሱስ ስለ ዕለታዊ እንጀራችን መጸለይ እንዳለብን ተናግሯል (ማቴዎስ 6፥11)። እግዚአብሔር በየቀኑ እንድንታመነው ይፈልጋል።
ያዕቆብ እግዚአብሔር ድሆችን በእምነት ባለ ጠጎች እንዳደረጋቸው ተናግሯል (ያዕቆብ 2፥5)። ድሆች የገንዘብ ዋስትና አለን ብለው ከሚያስቡ ሰዎች ይልቅ በእግዚአብሔር ላይ ለመደገፍ የተሻለ እድል አላቸው።
እግዚአብሔርን መታመን ሀላፊነት የጎደለን መሆን ማለት አይደለም። እግዚአብሔር በተለምዶ የሚሰጠን በስራችን ውስጥ ነው (ኤፌሶን 4፥28)። አንድ ሰው ለመሥራት ፈቃደኛ ካልሆነ እግዚአብሔር እንዲሰጠው መጠበቅ የለበትም፣ ሌሎች ሰዎችም ለእርሱ እንዲሰጡት መገደድ የለባቸውም (2ኛ ተሰሎንቄ 3፥10)።
የእግዚአብሔር አቅርቦት ባለጠጋ ያደርገናል ብለን መጠበቅ የለብንም። እግዚአብሔር ጥቂት ሰዎችን በሀብት ይባርካል ነገር ግን ሀብት ለሁሉም የእግዚአብሔር እቅድ አይደለም። ሀብትን አጥብቆ የሚፈልግ ሰው መንፈሳዊ ችግሮች ያጋጥመዋል።
ጠቃሚ ግብዓቶች ሰዎች እንዲያመርቱ የሚያግዟቸው ነገሮች ናቸው። ምሳሌዎች መሬት፣ የመሳሪያዎች ስብስብ ወይም ኮምፒውተር ናቸው። አንድ ሰው ጠቃሚ ግብአቶችን ተጠቅሞ ትርፍ ለማግኘት ይችላል ነገር ግን ግብአቱን ጠብቆ መያዝ አለበት እንጂ መሸጥ የለበት፣ አለበለዚያ ምርቱ ይቆማል። ስለ ጠቃሚ ግብአቶች መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማጣቀሻ ምሳሌ 14፥4 ነው “በሬዎች በሌሉበት በረቱ ባዶ ይሆናል፤ በበሬ ጕልበት ግን ብዙ ምርት ይገኛል”።
ድሃ ሰው የጠቃሚ ግብአቶችን ጽንሰ ሀሳብ ላይረዳ ይችላል። ለምሳሌ፣ ጓደኛው ውድ የሆኑ መሣሪያዎች፣ ኮምፒውተር ወይም ተሽከርካሪ ስላለው ብዙ ገንዘብ እንዳለው ሊገምት ይችላል። እንዲህ ያለ ነገር ያለው ጓደኛው ወይም ዘመዱ ገንዘብ ሲፈልግ ሊሰጠኝ ይገባል ብሎ ያስባል። ሆኖም ከእነዚህ ነገሮች ውስጥ ማንኛቸውም ሰውዬው ገቢውን ሳያሳጣው ሊሸጥ የማይችል ጠቃሚ ግብአት ሊሆን ይችላል።
► በአከባቢዎ ውስጥ ያሉ ሌሎች የጠቃሚ ግብአት ምሳሌዎች ምንድናቸው?
አንድ ሰው ጠቃሚ ግብአቶች ለሌሎች እንዴት እንደሚሰሩ ካልተረዳ ምን አይነት ግብአቶች በተመሳሳይ መልኩ ለእርሱ እንደሚሰሩ አያውቅም። እርሱ በጣም የሚፈልገውን በትክክል መናገር ወይም ምን ዓይነት እርዳታ ሁኔታውን እንደሚለውጥ በትክክል መናገር ላይችል ይችላል። እርዳታን ከእውነተኛ የህይወት ለውጥ ይልቅ በእለት ተእለት ጥረቶቹ ውስጥ ፈጣንና አጭር ማበረታቻን ሊገልጽ ይችላል።
አንዱ የድህነት ገጽታ የጠቃሚ ግብአቶች እጥረት ነው። በድህነት ውስጥ ያለ ሰው ጠቃሚ ግብአቶችን የማግኘት፣ የመንከባከብ እና የመጠበቅን አስፈላጊነት እስካልተማረ ድረስ ከጥገኝነት ሊወጣ አይችልም።
በአንዳንድ ባሕሎች አንድ ሰው ገንዘብን መቆጠብ እና ጠቃሚ ግብአቶችን ማዳበር አስቸጋሪ ይሆንበታል ምክንያቱም በዙሪያው ያሉ ሰዎች ሁሉንም ነገር እንዲካፈሉ ስለሚጠብቁ ነው። ሌላ ሰው ገንዘብ ሲፈልግ ለምን ገንዘብ እንደሚያከማች አይገባቸውም። ኃላፊነት የጎደላቸው ቢሆኑም እንኳ ያለውን እንዲካፈሉ ይጠብቃሉ።
የክርስቶስ ተከታይ ከባህሉ የሚጠበቀውን ማክበር አለበት ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱሳዊ መርሆችንም ተግባራዊ ማድረግ አለበት። መፅሐፍ ቅዱስ የሚችለውን ማድረግ የማይችለውን ሰው የመርዳት ግዴታ እንደሌለብን ይነግረናል (2ኛ ተሰሎንቄ 3፥10)። አንድ ሰው ኃላፊነት የጎደለውን ሰው ለመርዳት ጠቃሚ ግብአቱን ቢሰጥ ሁለቱም ድሆች ሆነው ይቆያሉ።
መፅሐፍ ቅዱስ የሚያመለክተው እግዚአብሔር የሚሰጠው የብልጽግና ዓይነት ለሰዎች የራሳቸው ጠቃሚ ግብአቶች እንዲኖራቸው ነው። ነቢዩ ሚክያስ በተባረከ ማህበረሰብ ውስጥ እያንዳንዱ ሰው የራሱን ወይንና የበለስ ዛፍ በአስተማማኝ ሁኔታ ይወርሳል (ሚክያስ 4፥4) ብሏል። ይህ የሚያመለክተው የግል ንብረት እና አንድን ነገር የማምረት መንገዶችን ነው። በአንዳንድ ቦታዎች ግብርና ምርጡ የምርት አይነት ላይሆን ይችላል ነገር ግን መርሆው የተባረኩ ሰዎች ግብአቶችን ለማምረት የሚያስፈልጋቸውን ነገር ማግኘት አለባቸው የሚል ነው።
ብዙ ጊዜ አማኝ የሆኑ ድሆች የበለጠ መበልጸግ ይጀምራሉ፤ በእግዚአብሔር ቀጥተኛ በረከት ብቻ ሳይሆን በተሻለ የአኗኗር ዘዴያቸው ነው። እንደ አልኮል፣ ቁማር እና የተሳሳቱ የመዝናኛ ዓይነቶች ላይ ገንዘብ ማባከን ያቆማሉ። እነርሱ የተሻሉ ሠራተኞች ይሆናሉ እናም የተሻለን ስም ያገኛሉ። እግዚአብሔር የአገልግሎት ድጋፋቸውን ይባርካል። ብዙውን ጊዜ የሁለተኛው የአማኝ ቤተሰብ ትውልድ ከመጀመሪያው ትውልድ በተሻለ ሁኔታ ውስጥ ነው።
► በአካባቢዎ ያሉ ሰዎች የፋይናንስ ሁኔታቸውን ለማሻሻል ሊሰሩ እና ሊቆጥቡ የሚችሉባቸው መንገዶች የትኞቹ ናቸው?
ቁማር በነጻነት ገንዘብ ለማግኘት በሚደረግ ሙከራ ገንዘብን አደጋ ላይ መጣል ነው። እያንዳንዱ ያሸነፈ ሰው በምላሹ ምንም ሳይሰጥ ከተሸነፈ ሰው ገንዘብ እየወሰደ ነው። ብዙ ሰዎች በቁማር ሱስ ይያዛሉ፣ ገንዘባቸውን ያባክናሉ እና ቤተሰቦቻቸውን መንከባከብ ያቅታቸዋል። ብዙ ሰዎች ለማሸነፍ እና መልሰው ለመክፈል ተስፋ በማድረግ የሌላ ሰው የሆነውን ገንዘብ ለቁማር ይጠቀማሉ። ቁማር ለመጫወት በሚል በስርቆት ወንጀል እስር ቤት የገብ ብዙ ሰዎች አሉ። በድህነት ውስጥ ያሉ ብዙ ሰዎች እድለኛ በመሆን እና ገንዘብን በማሸነፍ ካልሆነ በስተቀር ሁኔታቸውን ለመለወጥ ምንም ተስፋ እንደሌላቸው ስለሚሰማቸው ቁማር ይጫወታሉ።
ቁማር ከብዙ ክርስቲያናዊ መርሆዎች ጋር ይቃረናል፦
1. በሥራ ሀብት የማግኘት መርህ (ኤፌሶን 4፥28)
2. የመርካት መርህ (1ኛ ጢሞቴዎስ 6፥6)
3. የመዝራትና የማጨድ መርህ (ገላትያ 6፥7)
በተጨማሪም እግዚአብሔር በዕድል ከሌላ ሰው ገንዘብ ከመውሰድ ይልቅ አገልግሎትን ወይም ምርቶችን እንድንሰጥ ይፈልጋል። ቁማር ጎጂ ነው ምክንያቱም ሱስ የሚያስይዝ እና ወንጀልን የሚጨምር ነው።
ቁማር በእግዚአብሔር ላይ ከመታመን ጋር ተቃራኒ ነው። አንድ ሰው “እግዚአብሔር እንደሚንከባከበኝ አምናለሁን?” “እግዚአብሔር እንዲሰጠኝ መጸለይ እችላለሁን?” “እግዚአብሔር ለእኔ ሊያሟላልኝ የሚፈልገው መንገድ ገንዘብን ቁማር ለመጫወት ለአደጋ በማጋለጥ ከሌላው ገንዘብ በመውሰድ ነው ብዬ አምናለሁን?” “እግዚአብሔር ትልቅ መጠን እንዳገኝ በማድረግ በቁማር ዋጋ የሚከፍለኝ ይመስለኛልን?” ቁማር የሚጫወት ሰው በገንዘብ ሁኔታው እግዚአብሔርን አይታመንም። እግዚአብሔርን በእውነት ስንታመን ለእኛ ለሚሰጠው ግልጽ መመሪያዎች እንታዘዛለን፤ በምንታዘዝበት ጊዜ ፍላጎታችንን በታማኝነት እንደሚያሟላልን እናውቃለን።
አንድ ሰው ገንዘብ ሲበደር ወደፊት ከሚያገኘው ገንዘብ ሊከፍለው እንደሚችል ያስባል። ስለዚህ መበደር ማለት ወደፊት አዳዲስ ፍላጎቶችን ቢያመጣም ከወደፊቱ ገንዘብ ማውጣት ነው።
መጽሐፍ ቅዱስ ተበዳሪው የአበዳሪው አገልጋይ እንደሆነ ይናገራል (ምሳሌ 22፥7)። ተበዳሪ ነፃነቱን የሚገድቡ ግዴታዎችን ይፈጥራል።
አንዳንድ የብድር አይነት ከሌሎቹ የከፋ ነው። አንድ ሰው ለመሠረታዊ ፍላጎቶች ለምሳሌ ለምግብ ሲበደር ወደ ከፋ ሁኔታ እየገባ ነው። ምግቡ ይበላል፣ እዳውም ይይቆያል፣ እናም ከበፊቱ የበለጠ ድሃ ይሆናል።
አንድ ሰው ለማያስፈልግ ነገር ለምሳሌ ለግል ማጌጫ፣ ለአላስፈላጊ ልብስ፣ ለመዝናኛ ወይም ለቤት ማስዋቢያ ገንዘብ ሲበደር የወደፊት ገንዘቡን እያጠፋ ነው። የወደፊት ነፃነቱን እየገደበ ነው፤ ለወደፊቱ ገንዘቡ ቀድሞውኑ ስለጠፋ ነገሮችን ለመግዛት መምረጥ አይችልም።
አንዳንድ ቢዝነሶች በከፍተኛ ወለድ ብድር ይሰጣሉ። ከእነርሱ የተበደሩ ሰዎች ከመጀመሪያው ከተበደሩት የበለጠ ብዙ ዕዳ አለባቸው። አንዳንድ መደብሮች ነገሮችን በብድር በከፍተኛ የወለድ መጠን ይሸጣሉ። ሰዎች በመጨረሻ በዱቤ ለሚገዙት ነገር በጣም ከፍ ያለ ዋጋ ይከፍላሉ ምክንያቱም መደበኛውን ዋጋ ለመክፈል በቂ ገንዘብ እስኪያገኙ ድረስ ለመጠበቅ ፈቃደኛ አይደሉም።
አንዳንድ ጊዜ ሰዎች በባህላቸው የሚጠበቀውን ውድ የሰርግ ዝግጅት ለማቅረብ ገንዘብ ይበደራሉ። ትዳራቸውን የሚጀምሩት በታላቅ ዕዳ ነው። ቤተክርስቲያን እንደ እምነት ቤተሰብ አባሎቿን አዳዲስ ወጎችን በማዳበር ወይም ሠርግ እጅግ ውድ ሳይኾን የሚያምርበትን መንገድ በመፈለግ መርዳት አለባት።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ሮሜ 13፥7-8 ያንብብ።
እነዚህ ጥቅሶች ለሌሎች እንድንሰጥ የሚገባንን ይነግሩናል። ለባለሥልጣናት አክብሮት እና ታዛዥነት ማሳየት አለብን። ለመንግስት ግብር መክፈል አለብን። የቁጥር 8 የመጀመሪያው ዓረፍተ ነገር በቁጥር 7 ያሉትን መግለጫዎች ያጠቃልላል። ለማንም መስጠት ያለብንን መስጠት ሊሳነን አይገባም። ይህ ማለት ግን ፈጽሞ መበደር የለብንም ማለት አይደለም ምክንያቱም ከአበዳሪው ጋር በመስማማት መልሰን ከከፈልን መስጠት ያለብንን ከመስጠት አልጎደልንም።
አንድ ሰው ለመክፈል ሳያስብ መበደር እና በኋላ ላይ ላለመመለስ በመወሰን መበደር ስህተት ነው (መዝሙረ ዳዊት 37፥21)።
የብሉይ ኪዳን ሕጎች በአብዛኛው የተነገሩት ለእስራኤል ሕዝብ እንደ ጥንታዊ የግብርና ማህበረሰብ ነው። ብዙ ሰዎች የሚኖሩት በእርሻ እና በቤተሰቦቻቸው ውስጥ የሚያስፈልጋቸውን በማምረት ነው። ቤተሰቦች ለብዙ ትውልዶች አንድ አይነት መሬት በባለቤትነት ይይዛሉ። ስለዚህ አንድ ሰው መሬት ለመግዛት ወይም ንግድ ለመጀመር ገንዘብ መበደር ብርቅ ነገር ነበር። አንድ ሰው ገንዘብ ከተበደረ እርሱ በመጥፎ ሁኔታ ውስጥ ስለነበረ እና ለመሠረታዊ ፍላጎቶች ገንዘብ ስለሚያስፈልገው ነው። እግዚአብሔር እስራኤል ለአባላቶቹ እንክብካቤ የሚሰጥ የእምነት ቤተሰብ እንዲሆን ፈልጎ ነበር። እግዚአብሔር ወለድ ሳያስከፍሉ ለተቸገሩ ሰዎች ብድር እንዲሰጡ ነገራቸው (ዘጸአት 22፥25)። በመዝሙረ ዳዊት 15 ላይ የተገለጸው የጻድቅ ሰው መለያ አንዱ በወለድ ብድር አለመስጠቱ ነው (ሕዝቅኤል 18፥5-9 ከመዝሙረ ዳዊት 15 ጋር ይመሳሰላል)።
አንድ ባለሀብት አንድን ሰው ንግድ ለመጀመር እንዲረዳው ገንዘብ ሲያበድር ወለድ ቢያስከፍል ስህተት አይደለም (ማቴዎስ 25፥27)። ወለዱ ንግዱን እንዲሰራ ስላደረገ የባለሀብቱ ሽልማት ነው።
ከድሆች ጋር ቢዝነስን የሚሰሩ ሰዎች እንዴት ትርፍ ማግኘት እንደሚችሉ ማሰብ ብቻ የለባቸውም (ምሳሌ 22፥16)። ለድሆች ሌላ አማራጮች ስለሌላቸው ዝቅተኛ ጥራት ያላቸውን ምርቶች መሸጥ ወይም ፍትሃዊ ያልሆነ ዋጋ ማስከፈል ስህተት ነው። በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ምክንያት ብድር ከሚወስዱ ሰዎች ከፍተኛ ትርፍ ለማግኘት ብድር መስጠት ወይም ነገሮችን በብድር መሸጥ ስህተት ነው። አንድ የቢዝነስ ሰው የደንበኞቹን ሁኔታ ለማሻሻል መንገዶችን መፈለግ አለበት።
ነቢዩ ሕዝቅኤል የሰዶም ኃጢአት ዝሙት ብቻ ሳይሆን ሕዝቡ በቅንጦት ይኖሩ ነበር ነገር ግን ድሆችንና ችግረኞችን አይረዱም ነበር (ሕዝቅኤል 16፥49)። እግዚአብሔር የጠራን ለድሆች እንድንሰጥ ብቻ ሳይሆን እነርሱ እንዲጠነክሩ ስልታዊ በሆነ መንገድ እንድንረዳቸው ነው።
እግዚአብሔር ለጥንቷ እስራኤል የሰጣቸው ሕጎች ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ነገሮች ያሳዩናል። ዛሬ የሀገራችን ህጎች እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ከሰጣቸው ህግጋቶች ጋር አንድ አይነት አይደሉም ነገር ግን የእግዚአብሔር ስጋቶች እና መርሆቹ አንድ ናቸው። ቤተክርስቲያን ድሆችን የምታጠናክርበት፣ በመጀመሪያ የእምነት ቤተሰብን በመንከባከብ፣ ከዚያም በማህበረሰቡ ውስጥ ለውጥ ለማምጣት የሚያስችሉ መንገዶችን መፈለግ አለባት።
አንዳንድ ሰዎች ገንዘባቸውን ልክ እንዳገኙት ያጠፋታል። ብዙውን ጊዜ ገንዘብ ከማግኘታቸው በፊት በፍላጎት ይሰቃያሉ። ለሌሎች ሃላፊነት መውሰድ አይችሉም።
በጀት መደበኛ ወጪን የመቆጣጠር እቅድ ነው። ብዙ ሰዎች በተወሰነ ጊዜ የሚጠብቋቸው ወጪዎች አሏቸው እና ለእነዚያ ፍላጎቶች ገንዘብ አስቀድመው ማስቀመጥ አለባቸው። ለምሳሌ አንድ ሰው ቤት ሊከራይ ሊሆን ይችላል። በየወሩ ወይም በየዓመቱ ሊከፍል ይችላል። ጊዜው ሲደርስ ኪራይ ለመክፈል እንዲችል ከገቢው የተወሰነውን ክፍል በቋሚነት መቆጠብ ይኖርበታል። የቤት ኪራዩ አመታዊ ከሆነ ከገንዘቡ የተወሰነውን ለረጅም ጊዜ ይይዛል እና እርሱን ለመጠቀም ፈተና አለ ነገር ግን ገንዘቡን አስቀምጦ እንደጠፋ መቁጠር አለበት።
የመጀመሪያው መቀመጥ ያለበት ገንዘብ አሥራት መሆን አለበት (ምሳሌ 3፥9-10)። የገቢዎን 10% ለአገልግሎት ድጋፍ ለመስጠት ቃል መግባት አለቦት። ከወጪዎ በኋላ ለአሥራት ተጨማሪ ገንዘብ እንዳለዎት ለማየት አይጠብቁ። እግዚአብሔር ታማኝነትህን ይባርካል።[1]
መሠረታዊ ፍላጎቶቹ በቀሪው ገቢው ከተሸፈኑ በኋላ አንድ ሰው ለአደጋ ጊዜ ገንዘብ ማስቀመጥ ይኖርበታል። የራሱን ቤት ለመግዛት ገንዘብ መቆጠብን የመሰሉ ሁኔታውን ለማሻሻል የሚረዳ የተወሰነ ገንዘብ መያዝ ይኖርበታል። ገቢውን ለማሳደግ የተወሰነ ገንዘብ ለማፍሰስ መሞከር አለበት። የአንድ ትንሽ ኢንቬስትመንት ምሳሌ ለሥራ የበለጠ ክፍያ እንዲከፍል የሚያስችሉ መሳሪያዎችን መግዛት ሊሆን ይችላል።
እንደ ተሸከርካሪ ወይም ህንጻ ያሉ ጠቃሚ ግብአቶች (ለማምረት የሚረዳ ነገር) ያለው ሰው ሀብቱን ለመጠገን ገንዘብ መበጀት አለበት። አንድ ሰው በመኪናው ትርፍ ካገኘ ነገር ግን ገንዘብ ካላስቀመጠ ለትላልቅ የመኪና ጥገና መክፈል ወይም ሌላ መግዛት አይችልም እና ትርፉ በመጨረሻ ያበቃል።
በጀት የማያወጣ ሰው አብዛኛውን ጊዜ ኃላፊነቱን መወጣት ላይችል ይችላል። እርሱ ለእርዳታ በሌሎች ላይ ሊደገፍ እና ሌሎችን መርዳት ላይችል ይችላል። በምንም መልኩ ኢንቨስት ስለማያደርግ የእርሱ ሁኔታ ፈጽሞ አይሻሻልም።
ኢየሱስ የቆሰለውን ሰው ስለረዳው ደጉ ሳምራዊ ተናግሯል (ሉቃስ 10፥25-37)። ልብ በሉ ሳምራዊው ቁስለኛውን ለመሸከም የሚጠቀምበት ገንዘብና አህያ ነበረው። ሳምራዊው አህያውን ሸጦ ገንዘቡን ሁሉ አውጥቶ ቢሆንስ? ለመርዳት ጥሩ ፍላጎት ቢኖረውም በሁኔታው ውስጥ ጣልቃ የመግባት አቅሙ ውስን ይሆን ነበር።
በጀት ማውጣት አንድ ሰው ለፍላጎቱ እንዲዘጋጅ፣ በእርሱ ለሚተማመኑት ኃላፊነት እንዲወስድ፣ ለወደፊት ህይወቱ ኢንቨስት እንዲያደርግ፣ ለአደጋ ጊዜ ምላሽ እንዲሰጥ እና አገልግሎትን እንዲደግፍ ያስችለዋል።
በቤተክርስቲያን የመጀመሪያ ዘመን፣ ከጴንጤቆስጤ በኋላ ብዙም ሳይቆይ፣ አማኞች ለእምነት ቤተሰብ በጣም ቁርጠኞች ስለነበሩ የሁሉም ሰው ፍላጎቶች መሟላታቸውን ያረጋግጣሉ። ንብረታቸውን ተካፈሉ እንጂ ማንም የራሱ የሆነ ነገር እንደሆነ አልተናገረም። ብዙዎቹ ንብረት ሸጠው ገንዘቡን ለቤተክርስቲያን ሰጡ (ሐዋርያት ሥራ 2፥44-45)። ምንም እንኳን በቤተክርስቲያን ውስጥ ያለው ሕይወት ሁል ጊዜ እንደዚያ ይሆናል ብለን ባንጠብቅም፣ ቤተ ክርስቲያኒቱ በጥሩ ሁኔታ ላይ በምትገኝበት ጊዜ ልግስና እና ቤተሰብን ለመንከባከብ ቁርጠኝነት እንዳለ እናያለን።
የተሰሎንቄ አማኞች ሁሉም አባላት እንዲመገቡ እያደረጉ ነበር ነገር ግን አንዳንዶቹ እየሰሩ አልነበረም። እነዚያ ሰዎች በቤተክርስቲያኗ ልግስና ላይ በመመስረት በምቾት ይኖሩ ነበር። ጳውሎስ የቤተሰቡን አባላት መንከባከብን እንደተሳሳቱ ለቤተክርስቲያን አልነገራቸውም ነገር ግን አንድ ሰው ለመሥራት ፈቃደኛ ካልሆነ ምግብ ሊሰጠው እንደማይገባ ተናግሯል (2ኛ ተሰሎንቄ 3፥10)። ለአንዳንዶች ስራው ለደሞዝ ስራ ላይሆን ይችላል ነገር ግን እንደ አስፈላጊነቱ ሌሎች አማኞችን መርዳት ነው። አንዳንድ ሰዎች መቀጠር አይችሉም ነገር ግን ሁሉም ሰው ለመርዳት አንድ ነገር ማድረግ ይችላል።
በሌሎች ደብዳቤዎች ጳውሎስ መበለቶችን ለመርዳት እና ፓስተሮችን ለመደገፍ መመሪያዎችን ሰጥቷል (1ኛ ጢሞቴዎስ 5፥3-18፣ ገላትያ 6፥6)።
እያንዳንዱ አማኝ የአካባቢው የእምነት ቤተሰብ አካል መሆን አለበት እና የአባላቱን ፍላጎት ለመደገፍ እና አገልግሎቱን ለመርዳት ቁርጠኛ መሆን አለበት።
► ሰዎች ኃላፊነት እንዲወስዱ እየጠየቁ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያለውን ፍላጎት ለማሟላት እንዴት የቤተክርስቲያን ሰዎች በጋራ ሊሠሩ ይችላሉ?
► በአካባቢያችሁ የቤተክርስቲያን ሰዎች ጠቃሚ ግብዓቶችን ለማዳበር በጋራ እንዲሰሩ የሚያደርጉ ምን እድሎች አሉ?
የሰማይ አባት
ፍላጎቶቼን ለማሟላት ቃል ስለገባህልኝ አመሰግናለሁ። ራሴን እና በእኔ ላይ ለሚደገፉ ሌሎች ሰዎች ለማቅረብ ባለኝ ሃላፊነት ታማኝ እንድሆን እርዳኝ። ባለኝ ነገር ለጋስ እንድሆን እርዳኝ። የሌሎችን ፍላጎት በጥበብ እንዳሟላ እርዳኝ።
ለገንዘብ በረከቶች እጸልያለሁ፤ ከሁሉም በላይ ግን ከአንተ ጋር ባለኝ ግንኙነት መንፈሳዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ነገሮች ለመጠበቅ እና እርካታ ለማግኘት እፈልጋለሁ።
አሜን
(1) በዚህ ትምህርት ውስጥ የተሰጡትን መፅሐፍ ቅዱሳዊ መመሪያዎች በጸሎት አስቡባቸው። እያንዳንዱን የሚከተሉትን ጥያቄዎች በጽሁፍ ይመልሱ፦
ከገንዘብና ከሀብት ጋር በተያያዘ ምን ፈተናዎች አጋጥመውኛል?
በአሁኑ ጊዜ ገንዘብ እና/ወይም ግብአቶችን እንዴት አገኛለሁ?
ገንዘብን እና/ወይም ግብአቶችን እንዴት መጠቀም እና ማስተዳደር እችላለሁ?
እግዚአብሔርን በገንዘብ እና/ወይም በግብአቶች ማመን ማለት ምን ማለት ነው?
ምን ዓይነት ጠቃሚ ግብአቶች አሉኝ?
ወደፊት ለማግኘት ማቀድ ያለብኝ ጠቃሚ ግብዓቶች አሉን? ከሆነ ይህን እንዴት አደርጋለሁ?
ገንዘብ እና/ወይም ግብአቶችን ያላግባብ የተጠቀምኩት በምን መንገዶች ነው?
ከላይ የተዘረዘሩትን የገንዘብ እና/ወይም የግብአት አላግባብ አጠቃቀምን እንዴት ማስተካከል እችላለሁ?
(2) ከዚህ ትምህርት መርሆች ለአካባቢያችሁ ልዩ ማመልከቻዎችን በማድረግ ባለ 1 ገጽ የዝግጅት ፕረዘንቴሽን ይፃፉ። በአካባቢያችሁ ያሉ ሰዎች ስለ ገንዘብ ክርስቲያናዊ ግንዛቤ ምን መረዳት አለባቸው?
(3) ምሳሌ 3፥13-17ን ያሰላስሉ እና በእርሱም ላይ አንድ ገላጭ አንቀጽ ጻፍ። በሚቀጥለው የክፍል ጊዜ መጀመሪያ ላይ ይህንን የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል ከማስታወስ ይፃፉ እና አንቀጹን ለክፍል መሪ ይስጡት።
13 lessons · አማርኛ
Your print request has been recorded. Your download should begin shortly.
Download Print-Ready FileFree to print for ministry use. No changes to content, no profit sales.
SGC exists to equip rising Christian leaders around the world by providing free, high-quality theological resources. We gladly grant permission for you to print and distribute our courses under these simple guidelines:
All materials remain the copyrighted property of Shepherds Global Classroom.
Questions? info@shepherdsglobal.org
Total
$21.99Added to Cart!
By submitting your contact info, you agree to receive occasional email updates about this ministry.
Download audio files for offline listening
No audio files are available for this course yet.
Check back soon or visit our audio courses page.
Share this free course with others