የትምህርት ዓላማዎች
በዚህ ትምህርት መጨረሻ ተማሪው የሚከተሉትን ማድረግ ይኖርበታል፦
(1) እግዚአብሔር ለጋብቻ ያለውን እቅድ እና ከችግሮች የሚከላከሉ እና በረከቶችን የሚያቀርቡ የጋብቻ ደንቦችን መረዳት።
(2) ለቤተሰብ የመጽሐፍ ቅዱስ መመሪያዎችን ማብራራት።
Lesson
Playlist
Search through all lessons and sections in this course
Searching...
No results found
No matches for ""
Try different keywords or check your spelling
1 min read
by Stephen Gibson
በዚህ ትምህርት መጨረሻ ተማሪው የሚከተሉትን ማድረግ ይኖርበታል፦
(1) እግዚአብሔር ለጋብቻ ያለውን እቅድ እና ከችግሮች የሚከላከሉ እና በረከቶችን የሚያቀርቡ የጋብቻ ደንቦችን መረዳት።
(2) ለቤተሰብ የመጽሐፍ ቅዱስ መመሪያዎችን ማብራራት።
Dr. Robertson McQuilkin በጃፓን ሚስዮናዊ ሆኖ ለ12 ዓመታት አገልግሏል። በኋላም የColumbia International University ፕሬዚዳንት ሆነ። እርሱ ጸሐፊ፣ ተናጋሪ እና አስተማሪ በመሆን ይታወቅ ነበር። ሚስቱ Muriel በአልዛይመር በሽታ ትሰቃይ ነበር። ሕመሙ Muriel የማያቋርጥ እንክብካቤ ወደሚያስፈልጋት ሁኔታ ሲሸጋገር Dr. McQuilkin ሚስቱን ለመንከባከብ ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንትነት ተነሳ። ሲጋቡ የገባላትን ቃል እየፈፀመ እንደሆነ ተናግሯል። ሚስቱን መንከባከብ የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዝዳንትነት ቦታ ከመያዝ የበለጠ አስፈላጊ እንደሆነ ያምን ነበር።
ጋብቻ በእግዚአብሔር የተቋቋመው ለፈጠራቸው ለመጀመሪያዎቹ ወንድና ሴት ነው።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ዘፍጥረት 2፥21-24ን ያንብብ። እነዚህ ጥቅሶች ስለ ጋብቻ ምን ይነግሩናል?
ጋብቻ በእግዚአብሔር የተነደፈው ሰዎች እንደሚያስፈልጋቸው እንዲሆን ተደርጎ ነው። በትክክል የተነደፈው ለሰው ልጅ ተፈጥሮ ነው። እግዚአብሔር ባዘጋጀው ሁሉ እና በሚፈልገው ነገር ሁሉ ሁልጊዜ የሚበጀንን ይፈልጋል (ዘዳግም 6፥24)። እግዚአብሔር ለጋብቻ ያለው እቅድ ለእያንዳንዱ የትዳር ጓደኛ የተሻለ ስሜታዊ፣ ዝምድና እና መንፈሳዊ ደህንነትን እንደሚሰጥ ያውቃል።
ጋብቻ የእግዚአብሔር ባህሪ እና ግንኙነቶቹ ነጸብራቅ እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ ነው። እግዚአብሔር አብ፣ እግዚአብሔር ወልድ፣ እና እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እርስ በርሳቸው ሁልጊዜ በግንኙነት ነበሩ እናም ይኖራሉ። እያንዳንዱ በራሱ ሚና ልዩ ነው ነገር ግን ሁሉም የስላሴ አካላት በቋሚነት አንድ እና አንድ ማንነት ያላቸው ናቸው። በሥላሴ አካላት መካከል ባለው ግንኙነት፣ አንድነትን፣ መቀራረብን፣ ታማኝነትን እና ጽኑ ፍቅርን እናያለን። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጋብቻ በዚህ አስደናቂ ግንኙነት የተቀረጸ ነው። የእግዚአብሔር እቅድ እያንዳንዱ ባል እና ሚስት በፍቅራቸው ንፁህ እንዲሆኑ እና አንዳቸው ለሌላው ለህይወት እንዲሰጡ ነው።
እግዚአብሔር በትዳር ውስጥ አንድ ወንድና ሴት ወላጆቻቸውን ይተዋሉ እና ይተባበራሉ አለ። ጋብቻ ከየትኛውም የሰው ልጅ ግንኙነት የበለጠ ጠንካራ እና ቅርብ የሆነ ወዳጅነት እና አጋርነት ውስጥ ሁለት ሰዎችን ያስቀምጣል።
ጋብቻ በተወሰነ ግንኙነት ውስጥ ያሉ ሁለት ሰዎችን ብቻ የሚገልፅ አይደለም። ሕይወታቸው አንድ ሰው እንዲመስሉ በሚል ስሜት የተዋሃዱ እንዲሆኑ ተደርጓል። ይህ የየራሳቸውን ስብዕና ማጥፋት ሳይሆን ልዩ አንድነት ነው።
እግዚአብሔር ጋብቻን የፈጠረው ቋሚ እንዲሆን ነው። በትዳር ውስጥ አንድ ወንድና ሴት ሁለቱም በሕይወት እስካሉ ድረስ እርስ በርሳቸው ታማኝ ለመሆን ቃል ገብተዋል።
መጽሐፍ ቅዱስ ኢየሱስ ስለ ጋብቻ ከፈሪሳውያን ጋር በተደረገ ውይይት የተናገረውን መዝግቧል።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ማቴዎስ 19፥3-8ን ያንብብ።
ኢየሱስ ጋብቻ ቋሚ እንዲሆን የእግዚአብሔር ሀሳብ እንደሆነ ተናግሯል። ፍቺ የተፈጠረው እግዚአብሔርን ለማይከተሉ ሰዎች እንደሆነ ተናግሯል።
እግዚአብሔር ጋብቻን ዘላቂ እንዲሆን ያደረገባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ፣ አንዳንዶቹን በመጨረሻው ክፍል ተናግረናል። ትዳር ዘላቂ የሚሆንበት ሌላው ምክንያት ለልጆች ሲባል ነው። የእግዚአብሔርን የጋብቻ እቅድ መታዘዝ ልጆችን ለማሳደግ በጣም ጥሩውን አካባቢ ይፈጥራል። ወላጆች በትዳራቸው እና በቤተሰባቸው ውስጥ ለእግዚአብሔር መመሪያዎች በመታዘዝ እግዚአብሔርን ሲያከብሩ አምላካዊ ልጆችን ማሳደግ ይችላሉ (ሚልክያስ 2፥15)።
እግዚአብሔር የሰውን ሕይወት የፈጠረው ልጆች ወደ ጉልምስና ለማደግ ብዙ ዓመታት እንዲወስዱ በሚያስችል መንገድ ነው። በዚህ ጊዜ ልጆች ለጥበቃ፣ አቅርቦት እና ስልጠና በወላጆች ላይ ጥገኛ ናቸው። ይህ በአንድ ወይም በሁለት ዓመት ውስጥ ወደ ጉልምስና ከሚያድጉ እንስሳት የተለየ ነው። ሰዎች የበሰለ ባህሪን ለማዳበር ተጨማሪ ጊዜ ያስፈልጋቸዋል። እግዚአብሔር ቤተሰብን የፈጠረው ልጆችን የማሳደጊያ መንገድ አድርጎ ነው። በህብረተሰቡ ውስጥ ያሉ አብዛኛዎቹ ችግሮች ታማኝ ወላጆች ያሏቸው ቤተሰቦችን በማጣት የሚመጡ ናቸው።
ጋብቻ ሰዎች ሕይወታቸውን በሙሉ አንዳቸው ለሌላው ለመስጠት ቃል እንዲገቡ ይጠይቃል። ማንኛውም ባህል ጋብቻ ከባድ ቃል ኪዳን መሆኑን ለማሳየት ቅጾች እና ሥነ ሥርዓቶች አሉት። ሥነ ሥርዓቱ ወንድና ሴት ይህንን የዕድሜ ልክ ቁርጠኝነት እየፈጸሙ መሆናቸውን በይፋ የሚገልጹበት መንገድ ነው።
አብዛኞቹ መንግስታት የጋብቻ መዝገቦችን ይይዛሉ። የጋብቻ ሕጎች የንብረት ባለቤትነት፣ የልጆች ጥበቃ እና ውርስ ላይ ተጽእኖ ያሳድራሉ።
ለብዙ ሰርጎች ያገለገሉ የሰርግ መሀላዎች ምሳሌ እኚህ ናቸው፦
እኔ አንተን/ቺን [ባል/ሚስት] እንደ ሆንክ/ሽ ከዛሬ ጀምሮ ለመያዝ ተቀብያለሁ። በመልካምም ሆነ በክፉ ወቅት በባለጠግነትም ጊዜ ሆነ በድህነት፣ በሕመምም ሆነ በጤና፣ ሞት እስኪለያየን ድረስ ለመውደድ እና ለማክበር በእግዚአብሔር ቅዱስ ትዕዛዝ መሠረት ራሴን ለአንተ/ቺ እሳልፌ እሰጣለሁ።
የፍቅር ስሜት ሁል ጊዜ ቋሚ አይሆንም። ትዳር ሊለወጥ በሚችል የግል ስሜት ላይ የተመሠረተ ሊሆን አይችልም። የጋብቻ መሀላ ማለት አንድ ወንድና ሴት ሁለቱም በሕይወት እስካሉ ድረስ አንዳቸው ለሌላው ታማኝ ለመሆን ቃል ገብተዋል ማለት ነው እናም ይህ ተስፋ በማንኛውም ሁኔታ ላይ የተመካ አይደለም።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ 2ኛ ቆሮንቶስ 6፥14-18ን ያንብብ።
እነዚህ ጥቅሶች አማኝ ከማያምኑ ጋር በጣም የተቆራኘ ከሆነ ቁርጠኝነቱን እንደሚያስተጓጉል ይነግረናል። አማኝ ሰይጣንን ከሚያመልክ ሰው ጋር ማምለክ እንደማይችል ሁሉ የማያምኑትን አኗኗር እና ቅድሚያ ሊከተል አይችልም። ማስጠንቀቂያው የንግድ አጋርነቶችን ጨምሮ ለተለያዩ ግንኙነቶች ተፈጻሚ ሊሆን ይችላል።
ጋብቻ የሰው ልጅ የቅርብ አጋርነት ነው። አንድ አማኝ ቁርጠኛ አማኝ ያልሆነን ሰው ለማግባት ማሰብ የለበትም (1ኛ ቆሮንቶስ 7፥39፣ 2ኛ ቆሮንቶስ 6፥14-18)። ከማያምን ጋር የተጋባ አማኝ ልጆችን በማሳደግ እና የአኗኗር ውሳኔዎችን ለማድረግ ብዙ ሀዘን እና ብዙ መሰናክሎች ይገጥመዋል።
ባልና ሚስት ሁለቱም አማኞች ከሆኑ ነገር ግን ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት የመጡ ከሆኑ በመንፈሳዊ ጉዳዮች ላይ መስማማታቸውን ማረጋገጥ አለባቸው። ከተጋቡ በኋላ የአንድ የሀገር ውስጥ ቤተክርስቲያን አካል ለመሆን ማቀድ አለባቸው።
► ጋብቻ በፍቅር መግለጫ ብቻ ሳይሆን በመሀላ የሚጀመረው ለምንድን ነው?
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ዕብራውያን 13፥4 ያንብብ።
ይህ ጥቅስ ትዳር በጣም የተከበረ መሆን እንዳለበት ይነግረናል። ወሲባዊ ኃጢአት ጋብቻን አለማክበር ነው። እግዚአብሔር በወሲባዊ እርኩሰት ላይ ይፈርዳል።
የወሲብ ኃጢአት የፍትወት ምኞት፣ ዝሙት፣ ማመንዘር፣ ግብረ ሰዶም እና ፖርኖግራፊን ያጠቃልላል። የፍትወት ሀሳቦች መኖር የትዳር ጓደኛዎ ካልሆነ ከማንኛውም ሰው ጋር የግብረ ሥጋ ግንኙነትን በፈቃደኝነት ማሰብ ነው። ምንዝርና ባላገብ ሰዎች መካከል የሚደረግ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ነው። ዝሙት ሌላን ካገባ ሰው ጋር የሚደረግ የወሲብ ተግባርንም ያካትታል። ግብረ ሰዶማዊነት ተመሳሳይ ጾታ ባላቸው ሰዎች መካከል የሚደረግ የግብረ-ሥጋ ግንኙነት ነው። ፖርኖግራፊ እርቃንነትን ወይም ወሲባዊ እንቅስቃሴን በማሳየት የግብረ-ሥጋ ግንኙነትን ለመቀስቀስ የተነደፉ ጽሑፎችን፣ ምስሎችን እና ቪዲዮዎችን ያጠቃልላል። እነዚህ ሁሉ የጋብቻ ግንኙነቶችን የሚጥሱ ናቸው።
በሥጋ እኛን የሚያታልለን ረሃብ ሁሉ ከእግዚአብሔር በተሻለ ሊሟላልን የሚችለውን ፍላጎት መጠቀሚያ መሆኑን አስታውስ። የወሲብ ብቸኛው አምላካዊ አውድ የጋብቻ ወሲብ ነው። ያልተፈቀደ ወሲብ ለጊዜው ጣፋጭ ነው ነገር ግን በመጨረሻ የሚያጠፋንን እስከምንመኝ ድረስ መንፈሳዊ ፍላጎታችንን የሚመርዝ ነገር ነው። ያልተፈቀደ ወሲብ ለቅድስና፣ ለጽድቅ እና ለእግዚአብሔር በሕይወታችን መገኘት ያለንን ስሜት ከመቀነስ በቀር ምንም አያደርግም።[1]
በብዙ ምንባቦች ውስጥ የምሳሌ መፅሐፍ የፆታ ብልግና የሰውን ሕይወት እንደሚያጠፋ እና ወደ ሞት እንደሚመራ ያስጠነቅቃል (ምሳሌ 2፥16-19 እና ምሳሌ 6፥24-29፣ 32-33 ለምሳሌነት ይጠቀሳሉ)።
Robertson McQuilkin ሲጽፍ ለሰው ልጅ የግብረ ሥጋ ግንኙነት የእግዚአብሔር ዓላማዎች ከድርጊቱ ይልቅ በአዕምሮ ተጥሰዋል። ወንድ እና ሴት ብቻ አድርጎ አልፈጠራቸውም፤ እርስ በርሳቸውም በጠበቀ፣ በቋሚ ጋብቻ፣ በራሱ ተፈጥሮ የተነደፈ አንድነት ነው። ይህ ከፍተኛ ዓላማ ይፈጸም ዘንድ መቀራረቡ ብቸኛ እና በ በቁርጠኝነት ቋሚ መሆን አለበት አለበለዚያ አንድነት አይደለም። ታማኝነት ለአእምሮ በጣም አስፈላጊ ነው። ልዩ መቀራረብ፣ ቋሚ ቁርጠኝነት እና የጋራ መተማመን መጀመሪያ በአእምሮ ውስጥ ይጣሳሉ።[2]
► ተማሪዎች ለቡድኑ 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥9-11፣ 15-20 እና ማቴዎስ 5፥27-30 ማንበብ አለባቸው።
እያንዳንዱ ማህበረሰብ በወንዶች እና በሴቶች መካከል ስላለው ግንኙነት ባህላዊ እይታዎች አሉት። እነዚህ ባህላዊ አመለካከቶች ከመጽሐፍ ቅዱሳዊ የሥነ ምግባር ደረጃዎች ያነሰ ደረጃዎች አሏቸው። ብዙ ባህሎች ስርዓት ያለው ማህበረሰብን ለመጠበቅ አስፈላጊ የሆኑ ህጎች ብቻ አሏቸው። መጥፎ መዘዞችን ወይም ቅሌትን ለማስወገድ በጥንቃቄ ከተያዘ ወሲባዊ ኃጢአትን ይታገሳሉ። መጽሐፍ ቅዱሳዊው የሥነ ምግባር መለኪያ ግን የተለየ ነው።
በሚያሳዝን ሁኔታ አንዳንድ አብያተ ክርስቲያናት ከመጽሐፍ ቅዱስ ሥነ ምግባር ይልቅ የባሕላቸውን ሥነ ምግባር ይከተላሉ። ኃጢአታቸው ግልጽ የሆነ እና ግድ የለሽ የሆኑትን ሰዎች ይቀጣሉ ነገር ግን የበለጠ ጥንቃቄ በሚያደርጉ ሰዎች ተመሳሳይ ኃጢአቶች ሲኖሩ ይታገሳሉ።
እነዚህ ጥቅሶች እንደሚነግሩን እነዚህን ኃጢአቶች የሚሠሩ ሰዎች አማኞች እንዳልሆኑ እና ወደ መንግሥት ሰማይ እንደማይሄዱ ነው። አንዳንድ የቆሮንቶስ አማኞች እነዚህን ኃጢአቶች ቀደም ብለው ሰርተዋል ነገር ግን ከእነርሱ ድነዋል።
አማኝ ነኝ ለሚል ሰው ከእነዚህ ኃጢአቶች አንዱን ችላ የሚል ማንኛውም ትምህርት የውሸት አስተምህሮ ነው። አንድ ሰው የክርስቶስ ተከታይ ነኝ እያለ እና የፆታ ኃጢአት የሚሰራ ከሆነ ቤተክርስቲያን ከቤተክርስቲያን እንድታስወግደው እና እንደ አማኝ እንዳትቆጥረው በመፅሐፍ ቅዱስ ይጠበቅባታል (1ኛ ቆሮንቶስ 5፥11-13)።
የቤተክርስቲያን መሪዎች ጥሩ የባህሪ ምሳሌ መሆን አለባቸው። ቤተክርስቲያን የአምልኮ መሪዎችን ልክ ያልሆነ ልብስ እንዲለብሱ ስትፈቅድ ወይም በቤተክርስቲያን ውስጥ ስሜታዊ የሆኑ ጭፈራዎችን ስትፈቅድ፤ የተሳሳተ የፆታ ፍላጎት ችግር እንደሌለው እያመለከተች ነው። የጾታ ኃጢአት ከባድ እንዳልሆነ ያመለክታሉ።
የህብረተሰቡ የአለባበስ ዘይቤ አንድ ሰው የፆታ ስሜትን ለመሳብ አካላዊ ተጋላጭነት ከሌለው ጥሩ አለባበስ እንደሌለው ሊያመለክት ይችላል። የቤተክርስቲያኑ አባላት አንዳንድ ጊዜ በተለይም ለየት ባሉ አጋጣሚዎች በዚህ ስህተት ውስጥ ይወድቃሉ። የማህበረሰባቸውን ፋሽን እስካልተከተሉ ድረስ በደንብ ያልለበሱ ይመስላቸዋል። ቤተክርስቲያን ይህ ስህተት እንደሆነ ማስተማር አለባት። አንድ አማኝ በሌሎች ላይ የተሳሳተ ምኞት እንዲፈጠር መፈለግ የለበትም። 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥9-10 አማኞች የሚያያቸው ሁሉ ጥንቃቄ የተሞላበት፣ ንፁህ ህይወት እንደሚኖሩ እና ኃጢአት ለመስራት ወይም ሌሎችን እንዲሰሩ ለማድረግ ፈቃደኛ እንዳልሆኑ እንዲያውቅ መልበስ እና መሆን እንዳለባቸው ይነግረናል። ክርስቲያኖች በአክብሮት በሚለብሱ ልብሶች፣ በትሕትናና ራስን በመግዛት ማጌጥ አለባቸው።
ለኃጢአተኛ የሚሆን ረድኤት
ገላትያ 6፥1 ቤተክርስቲያን ሀጥያትን ያደረገውን አባል ለመመለስ የመሞከር ሃላፊነት አለባት ይላል። ይህ ማለት አንድ ሰው ኃጢአት ከሠራ በኋላ የአገልግሎት ሥልጣንን ይጠብቅ ወይም በፍጥነት ወደ አገልግሎት ቦታ ይመለሳል ማለት አይደለም። ተሐድሶ ማለት ወደ ቤተ ክርስቲያን ኅብረት እና እንክብካቤ መመለስ ማለት ነው። አባሉ በእውነት ንስሐ ከገባ፣ በእግዚአብሔር እና በቤተክርስቲያን ይቅር ይባላል። ድሉን እንዲጠብቅ እና በመንፈሳዊ ጠንካራ እንዲሆን ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ተጠያቂነትን መስጠት አለባት።
ያላገባች ሴት ልጅ ካረገዘች፣ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ተሐድሶን ሳትሞክር ከቤተ ክርስቲያን ኅብረት እና እንክብካቤ ልታስወግዳት አይገባም። ንስሐ ከገባች እና ለመንፈሳዊ ተጠያቂነት ከተገዛች ይቅርታ ይደረግላታል። የእርሷ ኃጢአት ከተሳሳተው ወንድ ሰው ኃጢአት የከፋ አይደለም። አንዳንድ ጊዜ ልጃገረዷ የኃጢአቷ ውጤት በግልጽ ስለሚታይ ብቻ በከፋ ሁኔታ ትያዛለች።
በአንዳንድ ማህበረሰቦች፣ ባላገባች ሴት ልጃቸው እርግዝና ምክንያት ሀፍረት የሚሰማቸው ወላጆች የቤተሰባቸውን ስም ለማዳን ሲሉ የተወለደውን ልጅ ለመግደል ይፈልጋሉ። ነገር ግን ለመግደል ምንም ጥሩ ምክንያት የለም (ዘጸአት 20፥13)። ያልተወለደ ህጻን ሁሉ በእግዚአብሔር መልክ ተፈጠረ (ዘፍጥረት 9፥6፣ መዝሙረ ዳዊት 139፥13-14)። ለልጅቷ ልጅ ጥበቃ፣ መወደድ እና እንክብካቤ መሰጠት አለበት።
ቤተክርስቲያን የእምነት ቤተሰብ ናት። ቤተ ክርስቲያን ኃጢአትን ማውገዟ ብቻ በቂ አይደለም። ቤተክርስቲያን አባሎቿን መንከባከብ አለባት። ለምሳሌ በኃጢአት ተግባር በገንዘብ የሚደገፍ ሰው አማራጭ የገንዘብ ድጋፍ ለማዳበር እርዳታ ሊፈልግ ይችላል።
ተጨባጭ ሁኔታ
ብዙ ሴቶች በአንድ ትልቅ ቤተ ክርስቲያን እየተካፈሉ በመዘምራን ቡድን ውስጥ እየዘመሩ ነበር። ቤተሰቦቻቸው ድሆች ነበሩ። ሴቶቹ ቤተሰቦቻቸውን ለመርዳት ሲሉ ገንዘብ ለማግኘት ከወንዶች ጋር ሥነ ምግባር የጎደለው ግንኙነት ነበራቸው። በዚህ ሁኔታ ቤተክርስቲያን ምን ማድረግ አለባት?
► ሰዎች ኃጢአተኛ የአኗኗር ዘይቤን እንዲተዉ ለመርዳት ቤተ ክርስቲያንዎ ምን ማድረግ አለባት?
ፖርኖግራፊ
ፖርኖግራፊ እርቃንን ወይም ወሲባዊ እንቅስቃሴን በማሳየት የግብረ-ሥጋ ግንኙነትን ለመፍጠር የተነደፉ ጽሑፎች፣ ሥዕሎች ወይም ቪዲዮዎች ናቸው።
በይነመረቡ ፖርኖግራፊን በአለም ዙሪያ በቀላሉ እንዲገኝ እያደረገ ነው። ፖርኖግራፊ፣ ቴክኖሎጂን በስፋት የመጠቀም ልምድ በጉዳዩ ላይ ክርስቲያናዊ መሠረታዊ ሥርዓቶችን ተግባራዊ እንዲያደርጉ ላልተማሩ ሰዎች ፈታኝ ሆኗል። ብዙ የበሰሉ ፓስተሮች እና መሪዎች እነዚያ ፈተናዎች በጭራሽ አላጋጠሟቸውም ምክንያቱም በወጣትነታቸው በይነመረብ የለም ነበር። ወጣቱ ትውልድ ምን እየገጠመው እንዳለ በጥቂቱ ብቻ ሊረዱት ይችላሉ።
ፖርኖግራፊ ስህተት ነው ምክንያቱም አንድ ሰው ዝሙትን፣ ምንዝርንና እና ብዙ ዓይነት የፆታ ብልግናን በዓይነ ሕሊናው እንዲያስብ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ በመሆኑ ስህተት ነው። የኃጢአት ምኞት ላለው ሰው ማራኪ ነው። ፖርኖግራፊ አንድ ሰው እግዚአብሔር በሚፀየፈው የሥነ ምግባር ብልግና ድርጊቶች እንዲደሰት ይጋብዛል።
ፖርኖግራፊ ሱስ የሚያስይዝ ነው። ፖርኖግራፊን የሚጠቀም ሰው በጣም ጠንካራ እርሱን የመፈለግ ስሜት ይሰማዋል። ያለ እርሱ መኖርን መገመት ይከብደዋል። ከፖርኖግራፊ ከሚያገኘው ምናብ ውጭ ሕይወት ባዶ እና ሳቢ እንደማይሆን ይመስለዋል። ልክ እንደሌላው ሱስ ምኞቶቹ ይወስዱታል እና ተጠቃሚው በህይወቱ ውስጥ ያሉትን መልካም ነገሮች መስዋዕት ማድረግ ይጀምራል።
ፖርኖግራፊ ሂደታዊ ነው። ተጠቃሚው ከጊዜ ወደ ጊዜ እጅግ በጣም ግልጽ እና ጠማማ የሆነ ቁሳቁስ ያስፈልገዋል። ከዚህ በፊት እርሱ በሚያስጠሉት እና በሚያስደነግጡት ምናቦች መደሰት ይጀምራል።
ፖርኖግራፊ ጎጂ ነው። ተጠቃሚው በተለመደው ግንኙነት የመደሰት አቅሙ ይቀንሳል። ፍላጎቶቹ ከተፈጥሮ ውጪ ስለሚሆኑ ፈጽሞ ሊረኩ አይችሉም። በሌሎች ላይ ለሚደርሰው በደል ቸልተኛ ይሆናል።
ፓስተሮች እና ወላጆች ወጣቶችን ስለ ሱስ አደገኛነት ማስጠንቀቅ አለባቸው። ወላጆች ልጆቻቸው ፈተናን ለመቋቋም ብስለት ስለሌላቸው ያልተገደበ የበይነ መረብ አጠቃቀምን መፍቀድ የለባቸውም። ፖርኖግራፊን የመመልከት ፈተናን የሚታገል ማንኛውም ሰው ስለ ድሎች ወይም ውድቀቶቹ ለታማኝና ፈሪሃ እግዚአብሔር ላለው ሰው በየጊዜው ሪፖርት ማድረግ ይኖርበታል። ከዚህ በሳል አማኝ ጋር የሚደረግ መደበኛ ምርመራ ታጋዩ ሰው ለንጽህና ያለውን ቁርጠኝነት እንዲጠብቅ እና የማያቋርጥ ድል እንዲያገኝ ይረዳዋል።
► ሰዎች ከፖርኖግራፊ ሱስ ይጠበቁ ዘንድ ምን ዓይነት ልማዶችን መምከር አለቦት? ቤተክርስቲያን እንዴት መርዳት ትችላለች?
የግብረ ሰዶማዊነት እንቅስቃሴ
መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥልጣንን የማይቀበሉ አንዳንድ ማህበረሰቦች የጋብቻ መጽሐፍ ቅዱሳዊ መግለጫንም አይቀበሉም። ሰዎች ተመሳሳይ ጾታዊ ግንኙነትን ለመምረጥ ነፃ ናቸው ይላሉ።
መጽሐፍ ቅዱስ ግብረ ሰዶምን ያወግዛል።
► ቡድኑ ሮሜ 1፥26-27፣ 1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥10 እና 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥9-10ን አንድ ላይ መመልከት ይኖርበታል።
እነዚህ ሦስት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች የግብረ ሰዶማዊነት ባህሪን በአንዳንድ የከፋ የኃጢአት ዓይነቶች ዝርዝር ውስጥ ያካትታሉ። እነዚህን ኃጢአቶች የሚከተሉ ሰዎች የእግዚአብሔርን ስልጣን ይቃወማሉ።
አንዳንድ ሰዎች በተፈጥሮ የግብረ ሰዶም ዝንባሌ እንዳላቸው ይናገራሉ። ምኞቶቻቸው እንዲኖራቸው ስላልመረጡ በባህሪያቸው ልንወቀስ አይገባም ይላሉ።
መጽሐፍ ቅዱስ እያንዳንዱ ሰው የኃጢአትን ተፈጥሯዊ ዝንባሌ እንደተከተለ ያስተምራል (ኢሳይያስ 53፥6)። በራሳችን ፈቃድ በምናደርገው ኃጢአት ንስሐ እንድንገባ እግዚአብሔር ጠርቶናል (ኢሳይያስ 55፥7)። በኃጢአተኛ ተፈጥሮ ስለተወለድን ተፈጥሯዊ ፍላጎቶቻችን ይመሩን ዘንድ ልናምናቸው አንችልም። አንድ ሰው ዝሙት ለመፈጸም፣ ወይም ጠበኛ ለመሆን ወይም ለመስረቅ የጠነከረ ተፈጥሯዊ ዝንባሌ ሊሰማው ይችላል ነገር ግን ተፈጥሯዊ ፍላጎት ትክክል ነው ማለት አይደለም።
በወሲባዊ ፍላጎት የተነሳ አንዳንድ ያላገቡ ሰዎች ማስተርቤሽን ያደርጋሉ። ማስተርቤሽን ማለት የጾታ ብልትን ለፆታዊ ደስታ ማነሳሳት ወይም የወሲብ ውጥረትን ማስታገስ ነው።
ፖርኖግራፊን መጠቀም ወይም በፈቃደኝነት የወሲብ ስሜት እርካታን መፍጠር ኃጢአት ነው (ማቴዎስ 5፥27-28፣ ማቴዎስ 15፥19-20)። መጽሐፍ ቅዱስ በተለየ ማስተርቤሽንን እንደ ሥነ ምግባር ብልግና አይኮንነውም። ይሁን እንጂ ግለ ወሲብ ወደ የዝሙት ሀሳብ፣ ፖርኖግራፊ መጠቀም እና ምንዝርና ሊመራ ይችላል።
ማስተርቤሽን ጥበብ የጎደለው ነው ምክንያቱም ሱስ የሚያስይዝ ነው። ብዙ ባደረጉት መጠን ብዙ ማድረግ እንዳለቦት ይሰማዎታል።
አስገዳጅ ማስተርቤሽንም ብዙውን ጊዜ ወደ ጥልቅ ስሜታዊ ወይም ግንኙነት ያሉ ችግሮች ወይም ቀደም ሲል የጾታ ጥቃት እንደደረሰበት ይጠቁማል።
► ተማሪዎች ለቡድኑ 1ኛ ቆሮንቶስ 6፥12-13፣ 18-20 እና 1ኛ ተሰሎንቄ 4፥1-8ን ማንበብ አለባቸው።
እግዚአብሔር በትዳር ውስጥ ሥጋዊ አንድነትን የፈጠረው ባልና ሚስት በስሜታዊና በመንፈሳዊ አንድ እንዲሆኑ ለመርዳት ነው (1ኛ ቆሮንቶስ 6፥16-20፣ ሚልክያስ 2፥15)።
ብዙዎች ማስተርቤሽን እስኪጋቡ ድረስ ብቸኝነታቸውን እንዲቋቋሙ እንደሚረዳቸው ያስባሉ። ነገር ግን ልምምዱ እየተለመደ ሲመጣ ወደፊት በትዳር ውስጥ ያለውን የፆታ ግንኙነት ውበት እና መቀራረብ አደጋ ላይ ሊጥል እንደሚችል መገንዘብ ተስኗቸዋል።
ግለ ወሲብ የወሲብን አስፈላጊ ዓላማ የሳተ የወሲብ ልምምድን ያቀርባል። በአካል እና በስሜታዊነት አንድ ስጋ ለመሆን የሁለቱን መዋሀድ ያስቀራል። ማስተርቤሽንን በትዳር ውስጥ ጤናማ እና ትክክለኛ የግብረ ሥጋ ግንኙነትን ምትክ አድርጎ መጠቀም የለበትም።[1]
አንድ ያላገባ ሰው ማስተርቤሽን በሕይወቱ ውስጥ ችግር ከሆነ ምን ማድረግ አለበት? ምንም እንኳን አንድ ሰው የወሲብ ውጥረትን ለማስታገስ ብቻ ማስተርቤሽን ቢያደርግም አሁንም ቢሆን ከፈተናዎች የተነሳ እና ግለ ወሲብ የእግዚአብሔርን የፆታ ግንኙነት አላማዎች ስለማያሳካ ማስወገዱ የተሻለ ነው።
በሕይወታቸው ውስጥ ምንም ዓይነት ብልግና ካለ ያንን ኃጢአት መናዘዝና መተው አለባቸው። ስለ ድሎች እና ውድቀታቸው ለሚፀልይላቸው እና ለሚያማክራቸው ፈሪሃ እግዚአብሔር ላለው ታላቅ መካሪ በየጊዜው እና በተደጋጋሚ መናገር አለባቸው።
ማስተርቤሽኑ በስሜታዊ ወይም በግንኙነት ችግሮች ወይም ያለፉ ወሲባዊ ጥቃቶች ውጤት ከሆነ ከፕሮፌሽናል ክርስቲያን አማካሪ ምክር ማግኘት ተገቢ ነው።
የክርስቶስ ተከታይ የሚረዳው በ፦
1. ኢየሱስ እንደሚያስብ በመተማመን (መዝሙረ ዳዊት 139፥1-3፣ 1ኛ ጴጥሮስ 5፥6-10)። ስለ እምነትህ፣ ለሥጋዊ ፍላጎቶችህ እና ስለ ንጽህናህ ያስባል። በሰብአዊነቱ፣ የሚገጥሙንን አካላዊ እና አእምሯዊ ፈተናዎች በድል አድራጊነት ተቋቁሟል እናም እኛ ድል እንድንቀዳጅ የሚያስፈልገን ጸጋ በእርሱ ዘንድ አለ (ዕብራውያን 4፥14-16)።
2. የዲያብሎስን ውሸት አለማመን (ዮሐንስ 8፥44)። ዲያብሎስ ኢየሱስ ግድ የለውም ቢሆን ኖሮ ላንተ አስቸጋሪ የሆነውን የወሲብ ፍላጎት ይወስደው ነበር በማለት ሊነግሮት ይችላል (1ኛ ጴጥሮስ 5፥7-8)። ዲያብሎስ የወሲብ ፍላጎት ስላለህ ኃጢአተኛ ነህ ብሎ ሊከስህ ይችላል (ራእ 12፥10)።
3. በኢየሱስ ላይ ማተኮር እና ስለ ማንነቱ ማመስገን (መዝሙረ ዳዊት 105፥3-4)። ዲያብሎስ እምነትህን እና ከእግዚአብሔር ጋር ያለህን ግንኙነት በዚህ ፈተና ሊያፈርስ ይይፈልጋል (ዮሐንስ 10፥10)። ነገር ግን ኢየሱስ ለዚህ ፈተና ያለው አላማ እምነታችሁ እንዲጠነክርና እርሱን ልታከብሩት እንድትችሉ ነው (1ኛ ጴጥሮስ 1፥5-9)። ኢየሱስን በማምለክ ላይ ስታተኩር እርሱ ሊረዳህ ይመጣል (መዝሙረ ዳዊት 46፥1)።
4. በእግዚአብሔር ቃል ላይ ማሰላሰል (መዝሙረ ዳዊት 119፥9)። የእግዚአብሔርን ቃል ማንበብ፣ ማዳመጥ እና ማሰላሰል በፈተና ጊዜ በድል ለመቆም ይረዳሃል። ኢየሱስ በተፈተነ ጊዜ ለማሸነፍ መፅሐፍ ቅዱስን ተጠቅሟል (ማቴዎስ 4)። እኛም እንዲሁ ማድረግ አለብን።
5. ቢያንስ በአንድ ጎልማሳ እና ፈሪሃ እግዚአብሔር ባለው ሰው በተጠያቂነት መያዝ (ገላትያ 6፥2)። ከአንተ በላይ በእምነት ጉዞ ላይ ላለ ሰው (የእርስዎ ተመሳሳይ ጾታ) ግልጽ እና ታማኝ መሆን በሚያስደንቅ ሁኔታ ጠቃሚ ይሆናል። እነርሱ ለእናንተ መጸለይ እና ምክር መስጠት ይችላሉ። ስለ ተጋድሎአችሁ ከእነርሱ ጋር መነጋገር ንጽህናን እንድትጠብቁ እና በእምነት እንድትበረታቱ ይረዳችኋል።
6. ሌሎችን ማገልገል እና በፍላጎታቸው ላይ ማተኮር (ፊልጵስዩስ 2፥3-5)። ሌሎች ሰዎችን በማገልገል ስለራስዎ ፍላጎቶች እና ምኞቶች ከመጠን በላይ መጨነቅን ይዋጉ።
7. በእግዚአብሔር ጊዜ አምላካዊ ከሆነ ሰው ጋር መጋባት (ምሳሌ 5፥15፣ 18-19)።
ወጣቶች ከማግባታቸው በፊት ከባድ ፈተናዎች ይገጥሟቸዋል። ታማኝ መሆን የሚችል የህይወት አጋር እንደሚያስፈልጋቸው ማስታወስ ለእነርሱ አስፈላጊ ነው።[1] ያለ ጋብቻ የአጭር ጊዜ ደስታን ለማግኘት ከሚፈልግ ሰው ጋር ያለውን ግንኙነት ግምት ውስጥ ማስገባት የለባቸውም። ቁርጠኛ ካልሆነ አማኝ ጋር ግንኙነት ለመፍጠር ማሰብ የለባቸውም (1ኛ ቆሮንቶስ 7፥39)። ታማኝ የትዳር አጋርና ጥሩ ወላጅ የሚሆነውን ሰው ብቻ ግምት ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
ጥሩ ትዳር ለመመሥረት የሚፈልግ ወጣት ትክክለኛ ሰው እንዲስብ ታማኝ እና ቁርጠኛ የሆነ የክርስቶስ ተከታይ መሆን አለበት (ምሳሌ 3፥4-8)። ሰው መልካም ምግባርን በተገቢው ባህሪ እና ልክን በመልበስ ያሳያል (1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥9-10)። ተቃራኒ ጾታ ካላቸው ሰዎች ጋር ግዴለሽነት የሚያሳዩ ሰዎች በመጥፎ ምኞቶች ላይ የተመሠረተ ግንኙነት ለመመሥረት ፈቃደኛ መሆናቸውን ያመለክታሉ (1ኛ ተሰሎንቄ 4፥1-7)። የተሳሳቱ ፍላጎቶችን በሚያስከትል መንገድ የሚለብስ ሰው የተሳሳተውን አይነት ሰው ይስባል (ምሳሌ 7)።
እግዚአብሔር ለወጣቶች ወላጆችን፣ ፓስተሮችን፣ እና ሌሎች ክርስቲያን መሪዎችን በባህሪ፣ በአለባበስ እና በግንኙነት ምርጫዎች ላይ መመሪያ እንዲሰጡ ሰጥቷቸዋል። ወጣቶች ለእግዚአብሔር በመታዘዝ ለእነዚህ መሪዎች ሲገዙ፣ የእግዚአብሔርን ታላቅ በረከት ያገኛሉ እናም ከብዙ ጉዳት እና ፈተና ይጠበቃሉ።
► ተማሪዎች ለቡድኑ 1ኛ ጴጥሮስ 5፥5 እና ዕብራውያን 13፥17ን ማንበብ አለባቸው።
ለወላጆቻቸው እና ለመንፈሳዊ ባለስልጣኖች ጥበብ እና አመራር መገዛት የልጆች ሀላፊነት ነው። ወጣቶች በፈተና በድል አድራጊነት እንዲኖሩ መርዳት የእነዚህ መሪዎች ኃላፊነት ነው።
► ተማሪዎች ለቡድኑ ሮሜ 13፥14 እና 1ኛ ቆሮንቶስ 10፥13ን ማንበብ አለባቸው።
እግዚአብሔር አማኞችን ለመቋቋም እና ፈቃደኛ ከሆኑ ሊያመልጡ ከሚችሉት በላይ በፈተና ሁኔታዎች ውስጥ እንዲሆኑ አይፈቅድም። ወጣቶች ፈተናን የመሸሽ ሃላፊነት አለባቸው (2ኛ ጢሞቴዎስ 2፥22)። ይሁን እንጂ ወላጆች በተቻለ መጠን ወጣቶች አላስፈላጊ ፈተና እንዳይደርስባቸው መከላከል አለባቸው። ወላጆች ይህን የሚያደርጉበት ቢያንስ ሦስት መንገዶች አሉ፦
(1) የተለየ መመሪያ በመስጠት ልጆቹ ምን ማድረግ እንዳለባቸውና እንደሌለባቸው፣ ከማን ጋር መሆን እንዳለባቸው እና የት መሄድ እንዳለባቸው የተለየ መመሪያ በመስጠት (ኤፌሶን 6፥1-4)።
ልጆቻቸው ከፈተና ራሳቸውን ለመጠበቅ ብስለታቸው በቂ በማይሆንባቸው ሁኔታዎች ውስጥ እንዲሆኑ ወላጆች መፍቀድ የለባቸውም። ለምሳሌ፣ አንድ ወጣት ወንድና ወጣት ሴት ብቻቸውን በግል ቦታ ላይ ከሆኑ መጥፎ ባህሪ እንዲያሳዩ ሊፈተኑ ይችላሉ።
(2) ወጣቶቻቸው በፈተና አካባቢዎች ተጠያቂ እንዲሆኑ በማድረግ።
(3) ለወጣቶች መጽሐፍ ቅዱሳዊ ምክርን በመስጠት።
ወጣቶች የመጽሐፍ ቅዱስን መሠረታዊ ሥርዓቶች በማሰብ ሁኔታዎችን እንዲያጤኑ ወላጆች እየረዷቸው መሆን አለባቸው (ምሳሌ 4፥1-9፣ ምሳሌ 7፥1፣ 4-5)። ስለሚያዩት አደጋ ከወጣቶች ጋር መነጋገር አለባቸው። ወጣቶቻቸው ማድረግ የሚፈልጓቸውን የተለያዩ ምርጫዎች እንዲያስቡ መርዳት አለባቸው። ፈተናዎችን እንዴት ማስወገድ እንደሚችሉ እና ፈተናዎች ሲያጋጥሟቸው ደግሞ ምን ማድረግ እንዳለባቸው አስቀድሞ እንዲያስቡ ሊረዷቸው ይችላሉ።
ቤተ ክርስቲያን ለመጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥነ ምግባርን ስትቆም ከባህሏ የተለየ መሆን አለባት። ብዙ ባህሎች ወሲባዊ ኃጢአትን እንደ ከባድ አድርገው አይቆጥሩትም። ወጣት ያላገቡ ሰዎች ከጋብቻ በፊት የግብረ ሥጋ ግንኙነት እንዲፈጽሙ ይጠብቃሉ። ቤተ ክርስቲያን ከኃጢአት ጋር መደራደር የለባትም። ቤተክርስቲያን በወጣቶች መካከል ያለው የወሲብ ኃጢአት የተለመደ ነው ብላ ማሰብ የለባትም። እግዚአብሔር ሴሰኞች በክርስቶስ መንግሥት ርስት የላቸውም ይላል።
► ተማሪዎች ለቡድኑ ኤፌሶን 5፥3-7 እና ዕብራውያን 13፥4ን ማንበብ አለባቸው።
ከጋብቻ በፊት ያለው ግንኙነት የግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚጀመርበት ጊዜ አይደለም። ይልቁንም ወንድና ሴት አንድ ዓይነት መንፈሳዊ እና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን ነገሮች መካፈላቸውን የሚያረጋግጡበት ጊዜ ነው። እርስ በርስ መረዳዳትን የሚያዳብሩበት ጊዜ ሲሆን ይህም እርስ በርስ ለመተማመኛ የሚሆን ዘላቂ ቁርጠኝነት እንዲኖር ያደርጋል። አንዳቸው የሌላውን ባህሪ ወደዚህ እምነት ማምጣት ካልቻሉ ግንኙነታቸውን ማቆም እና ማግባት የለባቸውም።
በአንዳንድ ማህበረሰቦች ውስጥ ያሉ ሰዎች ጋብቻን የሚያንጓትቱት ባህላቸው ጋብቻ በጣም ውድ የሆነ ሥነ ሥርዓት እንዲሆን ስለሚጠበቅ ነው። ብዙ ጊዜ ጥንዶች ለዓመታት አብረው ይኖራሉ እና ትዳርን በሚያዘገዩበት ጊዜ ልጆች ይወልዳሉ። አንዳንድ ጥንዶች ለሠርጋቸው የሚያወጡት ወጪ ለረጅም ጊዜ በገንዘብ ይጎዳቸዋል ምክንያቱም ለሠርጉ ዝግጅት ያላቸውን ሁሉ ስለሚያወጡ እና ምናልባትም ገንዘብ ሊበደሩ ስለሚችሉ ነው። ቤተ ክርስቲያን የተለየ የጋብቻ ሞዴል የምትሰጥ የእምነት ማኅበረሰብ መሆን አለባት። ክርስቲያናዊ ጋብቻ እራስ በራስ እንዲሁም በእግዚአብሔር ፊት ቁርጠኛ ለሆኑ ወንድና ሴት የተሰጠ ነው እና ሠርጉን የሚያዘገይ ወይም የተጋቢዎችን የወደፊት ሕይወት የሚጎዳ ትልቅ ወጪ ሊጠየቁ አይገባም።
► ክርስቲያናዊ ጋብቻ ከኅብረተሰቡ የጋብቻ ባሕሎች የሚለይባቸው አንዳንድ መንገዶች የትኞቹ ናቸው?
ጋብቻ ለብዙ ሰዎች የእግዚአብሔር እቅድ ነው። ይሁን እንጂ ሐዋርያው ጳውሎስ ሰዎች የማያገቡባቸውን አንዳንድ ምክንያቶች ገልጿል። 1ኛ ቆሮንቶስ 7፥26 ላይ ስደትን ሊያካትት የሚችለውን አስቸጋሪ የህይወት ሁኔታዎች ጠቅሷል። እንዲህ ባሉ ሁኔታዎች ውስጥ አለማግባት የተሻለ ሊሆን ይችላል ብሏል።
ይኸው ክፍል (1ኛ ቆሮንቶስ 7፥32-35) ያላገባ ሰው ልዩ ጥቅም እንዳለው ይናገራል። ያላገባ ሰው የትዳር ጓደኛን የመንከባከብ ጉዳይ ሳያስብ እግዚአብሔርን በማገልገል ላይ ሊያተኩር ይችላል። ሰው ሳያገባ በአገልግሎት ላይ እንዲያተኩር በእግዚአብሔር ከተጠራ፣ በአገልግሎቱ በሚያስደንቅ ሁኔታ ውጤታማ እና የተባረከ ሊሆን ይችላል።
እግዚአብሔር አንድ ሰው ሳያገባ እንዲቀር የሚመርጥባቸው ሌሎች ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ (ማቴዎስ 19፥10-12)። ይህ ከተፈጥሮ ውጪ የሆነ ሁኔታ ነው ብለን ማሰብ የለብንም። እያንዳንዱ ያላገባ ሰው ከአንድ ሰው ጋር መዛመድ አለበት ብለን ማሰብ የለብንም። ደስታና እርካታ በትዳር ላይ የተመካ ነው ብለን ማሰብ የለብንም (መዝሙረ ዳዊት 107፥9)።
ያላገባ ሰው በስሜታዊ እና በአካላዊ ፍላጎቶች ምክንያት የተሳሳተ ግንኙነት እንዳይፈጥር መጠንቀቅ አለበት። እግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ ለእርሱ ላደረ ሰው ደስታን እና እርካታን ይሰጣል።
► 1ኛ ጴጥሮስ 3፥1-7 እና ኤፌሶን 5፥22-33ን አንድ ላይ አንብቡ። ቡድኑ በዚህ ውይይት ወቅት እነዚህን ምንባቦች ለመመርመር ክፍት ማድረግ አለበት።
ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን እንደወደደ ሰው ሚስቱን እንዲወድ ተነግሮታል። ኢየሱስ ራሱን ለቤተ ክርስቲያን መሥዋዕት አድርጎ ሰጠ። ባል የሚስቱን ፍላጎት ለማሟላት የራሱን ጥቅም፣ ምቾት እና ፍላጎት መስዋዕት ማድረግ አለበት። 1ኛ ጴጥሮስ 3፥7 ከሚስቱ ጋር በመግባባት ይኑር ይላል ይህም ማለት እርሷን ለመረዳት የተቻለውን ሁሉ ማድረግ ነው። ፍላጎቷን ለመረዳት እርሷን ማጥናት አለበት።
ሴቲቱ በዚህ ክፍል ውስጥ “ደካማ ዕቃ” ተብላለች። ሚስት ከባሏ ትኩረት ያስፈልጋታል። እርሷን ከአካላዊ ጉዳት ብቻ ሳይሆን ከስጋት እና ከስሜታዊ ጭንቀትም ሊጠብቃት ይገባል።
ሚስት ለባሏ እንድትገዛ እና እንድታከብረው ተነግሯታል። ሚስት ባሏ አማኝ ባይሆንም የባሏን አመራር መቀበል አለባት። ይህን ካደረገች ያልዳነ ባሏ አማኝ የመሆን እድሉ ሰፊ ነው።
በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ ያሉት ትዕዛዞች እንዴት እንደተሰጡ ማስታወስ አስፈላጊ ነው። ባል በሚስቱ ላይ ሥልጣንን እንዲያስገድድ አይነገረውም። ሚስት ባሏን እንድትታዘዝ ተነግሮአታል ነገር ግን ባልዋ እንድትታዘዝ እንዲያደርጋት አልተነገረም። ሚስቱን እንዲወድ እና እርሷን ለመንከባከብ መስዋዕትነት አስፈላጊ እንደሆነ ተነግሮታል። በተመሳሳይም ሚስት ከባሏ እንክብካቤ እንድትጠይቅ አልተነገራትም፣ እንድታከብረው ተነግሯታል።
ለባል ቅድሚያ የሚሰጠው ሥልጣኑን ማስጠበቅ ሳይሆን ፍቅራዊ እንክብካቤን መስጠት ነው። ለሚስት ቅድሚያ የሚሰጠው ለራሷ እንክብካቤ መጠየቅ ሳይሆን ባሏን ማክበር ነው።
ሐዋርያው ባል ለሚስቱ ተገቢውን እንክብካቤ ካላደረገ ጸሎቱ እንደሚገታ ያስጠነቅቃል። ይህ በትዳር ውስጥ ያለን ባህሪ ከእግዚአብሔር ጋር ባለን ግንኙነት ላይ ተፅዕኖ እንደሚያደርግ ይነግረናል።
ሐዋርያው ዮሐንስ አንድ ሰው ወንድሙን የማይወድ ከሆነ እግዚአብሔርንም አይወድም (1ኛ ዮሐንስ 4፥20) ብሏል። በተመሳሳይም ከጳውሎስና ከጴጥሮስ ቃል የምንረዳው ሰው ሚስቱን እንደሚገባ የማይንከባከብ ከሆነ እግዚአብሔርን እንደሚገባው መውደድ አይችልም። ባሏን የማታከብር ሴት እግዚአብሔርን ማክበር እንደሚገባት አታከብርም።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ 1ኛ ቆሮንቶስ 7፥1-5 ያንብብ።
እነዚህ ጥቅሶች የጋብቻ አንዱ ዓላማ የወሲብ ፍላጎትን ማርካት እንደሆነ ይነግሩናል። ባልና ሚስት እራሳቸውን አንዳቸው ለሌላው አሳልፈው ሰጥተዋል እና በገዛ አካላቸውበ ላይ ያላቸውን ባለቤትነት ትተዋል። ይህ ማለት አንድ ያገባ ሰው በመረጠው ጊዜ ብቻ የግብረ ሥጋ ግንኙነት እንደሚፈጽም መጠበቅ የለበትም ነገር ግን ለትዳር ጓደኛው ፍላጎትም ጭምር ምላሽ መስጠት አለበት። አንድ ሰው ከትዳር ጓደኛው ፈቃድ ውጭ እርካታን ሊጠይቅ እንደሚችል ጥቅሶቹ አይነግሩንም። ይልቁንም ጥቅሶቹ እያንዳንዳቸው ለሌላው ፍላጎት ምላሽ እንዲሰጡ ይነግራቸዋል።
ይህ ክፍል የተጋቡ ሰዎች አንዳቸው ሌላውን ይህንን መብት መከልከል እንደሌለባቸው ይነግረናል። ከፆም ጋር ለአጭር ጊዜ የግብረ ስጋ ግንኙነት መከልከል ትክክል ነው ነገር ግን ረጅም መለያየት ከፍላጎቶች የተነሳ ፈተናን ያስከትላል። አንዳንድ ጊዜ ባለትዳሮች አንዳቸው ወደ ሥራ ወይም ሩቅ ቦታ ለጥናት ስለሚሄዱ ለብዙ ወራት ወይም ከዚያ በላይ መለያየትን ይመርጣሉ። እንዲህ ዓይነት ውሳኔ ከማድረጋቸው በፊት እንዲህ ዓይነቱ ዕቅድ ከእግዚአብሔር ዕቅድ ጋር የሚስማማ መሆኑን ወይም አለመሆኑን ግምት ውስጥ ማስገባት አለባቸው። ለረጅም ጊዜ በመለያየት ምክንያት ችግር ሊገጥማቸው ይችላል።
አንዱ የጋብቻ አላማ ለአባሎቻቸው ማቅረብ የሚችሉ ቤተሰቦችን መፍጠር ነው።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ 1ኛ ጢሞቴዎስ 5፥8 ያንብብ።
ይህ ጥቅስ የቤተ ክርስቲያን አባላት እርስ በርስ የመተሳሰብ ኃላፊነትን በሚገልጽ ምንባብ ውስጥ ይመጣል። የአንድ ሰው የመጀመሪያ ኃላፊነት የራሱ ቤተሰብ ነው። ወላጆች እንደ መጠለያ፣ ምግብ፣ ልብስ እና ትምህርት ያሉ የልጆቻቸው ፍላጎቶች መሟላታቸውን ማረጋገጥ አለባቸው። ወላጆች ይህንን ኃላፊነት ለሌሎች ከመተው ይልቅ ለማቅረብ የሚችሉትን ሁሉ ማድረግ ይኖርባቸዋል።
በዚህ ትምህርት ውስጥ ያሉት ርዕሶች ብዙ ውይይት ይፈጥራሉ።
ተማሪዎቹ የዚህን ትምህርት መፅሐፍ ቅዱሳዊ መርሆች በራሳቸው ሁኔታ ላይ ለመጠቀም መሞከር አለባቸው።
► ብዙ ሰዎች የሚረሱት ስለትዳር ያለው እውነት ምንድን ነው?
► ከዓለም ፈተናዎች ጋር እየታገሉ ያሉትን ወጣቶች ቤተ ክርስቲያን እንዴት ልትረዳቸው ትችላለች?
► ሕፃናት ክርስቶስን እንዲከተሉ የማሰልጠን ተግዳሮትን ለመርዳት የቤተ ክርስቲያን ሰዎች (ከሰንበት ትምህርት ቤት መኖር ባለፈ) እንዴት አብረው ሊሠሩ ይችላሉ?
የሰማይ አባት
ስለ አስደናቂ የጋብቻ ንድፍህ እናመሰግናለን። በሁሉም የሕይወቴ ደረጃዎች ለፈቃድህ ታማኝ እንድሆን እርዳኝ። ለክርስቲያን ታማኝነት ጥሩ ምሳሌ እንድሆን እርዳኝ። ሌሎች የአንተን ፈቃድ እንዲከተሉ እንዳበረታታ እርዳኝ።
ቤተሰቦችን፣ ወጣቶችን እና ልጆችን በእምነት እና በታዛዥነት እንዲጠነክሩ ለመርዳት በቤተክርስቲያን ውስጥ እንድተባበር እርዳኝ።
የምትባርከው ግንኙነት እንዲኖረን ስለሰጠኸን ዕድል እናመሰግናለን።
አሜን
(1) ያላገባህ ከሆንክ ከጋብቻ በፊት ለምትኖረው ግንኙነትና ለወደፊት ትዳርህ የእግዚአብሔርን መሠረታዊ ሥርዓቶች ለመታዘዝ ቃል ኪዳን የምትገባበትን ሁለት አንቀጾች ጻፍ። ያገባህ ከሆንክ ለትዳርህ የእግዚአብሔርን መሠረታዊ ሥርዓቶች ለመታዘዝ ቃል ኪዳን የምትገባበት ሁለት አንቀጾች ጻፍ።
(2) ከዚህ ትምህርት አንድ ወይም ከዚያ በላይ ርዕሶችን ምረጥ እና አንድ ሰው በማኅበረሰብህ ውስጥ መፅሐፍ ቅዱሳዊ መመሪያዎችን እንዴት ተግባራዊ እንደሚያደርግ የሚገልጽ ገጽ ጻፍ።
ምሳሌዎች
በማህበረሰብህ ውስጥ ለማግባት ባሰቡ ወንድና ሴት መካከል ያለውን ክርስቲያናዊ ግንኙነት ግለጽ።
በማህበረሰብዎ ውስጥ ለትዳር ታማኝነት ማሳየት የሚፈልግ ወንድ ወይም ሴትን ባህሪ ይግለጹ።
13 lessons · አማርኛ
Your print request has been recorded. Your download should begin shortly.
Download Print-Ready FileFree to print for ministry use. No changes to content, no profit sales.
SGC exists to equip rising Christian leaders around the world by providing free, high-quality theological resources. We gladly grant permission for you to print and distribute our courses under these simple guidelines:
All materials remain the copyrighted property of Shepherds Global Classroom.
Questions? info@shepherdsglobal.org
Total
$21.99Added to Cart!
By submitting your contact info, you agree to receive occasional email updates about this ministry.
Download audio files for offline listening
No audio files are available for this course yet.
Check back soon or visit our audio courses page.
Share this free course with others