የትምህርት ዓላማዎች
በዚህ ትምህርት መጨረሻ ተማሪው በማንኛውም ጊዜ በሁሉም ሁኔታዎች ውስጥ ፍጹም ታማኝ ለመሆን ቃል መግባት አለበት።
Lesson
Playlist
Search through all lessons and sections in this course
Searching...
No results found
No matches for ""
Try different keywords or check your spelling
1 min read
by Stephen Gibson
በዚህ ትምህርት መጨረሻ ተማሪው በማንኛውም ጊዜ በሁሉም ሁኔታዎች ውስጥ ፍጹም ታማኝ ለመሆን ቃል መግባት አለበት።
አብርሃም በአንድ ሱቅ ውስጥ ይሠራ ነበር። አንድ ቀን ለደንበኛው ትክክለኛውን የገንዘብ ለውጥ እንዳልሰጠ ተገነዘበ። ሴትየዋ ቀድማ ሄዳ ነበር። ብዙ ኪሎ ሜትሮች ርቃ የምትኖረው በገጠር አካባቢ ነው እና አብርሃም በቅርቡ እንደማያገኛት ያውቅ ነበር። የገንዘቡ መጠን ትንሽ ቢሆንም ምናልባት ለእርሷ ሊያስፈልጋት እንደሚችል አሰበ። እንዲሁም ገንዘቧን ሆን ብሎ ያስቀረ እንዳይመስላት ፈልጎ ነበር። ሱቁ ለእለቱ ሲዘጋ አብርሃም ገንዘቡን ለመመለስ ብዙ ኪሎ ሜትሮች ተጉዟል። በዚያ እና በሌሎች ሁኔታዎች ባለው ጥንቃቄ ጓደኞቹ “ታማኝ አቤ” ብለው ይጠሩታል። በኋላ የሕግ ባለሙያ ሆነ ከዚያም በመንግሥት ሥራ ውስጥ ገባ። በሐቀኝነቱ የተከበረ ነበር እና በመጨረሻም የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ሆኖ አገልግሏል።
መጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር ሊዋሽ እንደማይችል ይነግረናል (ቲቶ 1፥2፣ ዕብራውያን 6፥18)። ተፈጥሮው ሁል ጊዜ ቀጣይ እና የማይለወጥ ነው (ያዕቆብ 1፥17)። እግዚአብሔር እውነትን የሚናገረው ጥቅም ሲሰጥ ብቻ አይደለም። ጥሩ ውጤት ለማግኘት አይዋሽም። የእግዚአብሔር ቃል ፍጹም እውነት እና እምነት የሚጣልበት ስለመሆኑ እርግጠኞች ልንሆን እንችላለን። የእርሱ እውነት ደህንነትን ይሰጠናል (መዝሙረ ዳዊት 40፥11፣ መዝሙረ ዳዊት 91፥4)።
► ምንጊዜም እውነትን እንደሚናገር ካላመንክ ከእግዚአብሔር ጋር ባለህ ግንኙነት ምን ተጽዕኖ ይኖረዋል?
እውነት ከእግዚአብሔር ጋር ላለን ግንኙነት እንዴት አስፈላጊ እንደሆነ አስቡ። ሙሉ በሙሉ ለእርሱ እንድንሰጥ እግዚአብሔር ጠርቶናል። እርሱን ሙሉ በሙሉ ካላመንን ያንን ማድረግ አንችልም።
እግዚአብሔር ሁል ጊዜ እውነቱን እንድንናገር ይፈልጋል። ውሸትን የሚናገር ሰው በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ አይደለም (ምሳሌ 12፥22)።
አንዳንድ ጊዜ ሰዎች በፍርድ ቤት ጉዳዮችን ለማሸነፍ ውሸትን ይጠቀማሉ። ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ከሌሎች ንብረትን ለመውሰድ ሲሉ ዳኛ ውሸትን እንዲቀበል መክፈል ይችላሉ (ያዕቆብ 2፥6)። ባለጠጎች ከፍትህ ያመልጣሉ እና ንፁህ ሰዎችን ለመውቀስ ውሸትን ለመፍጠር ጉቦ ይከፍላሉ (ያዕቆብ 5፥1፣ 6)።
ምክንያትህ ትክክል ነው ብለህ ብታስብም በውሸት መመስከር ኃጢአት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የሐሰት ምስክሮችን ያወግዛል እናም ልዩ ሁኔታዎችን አይፈቅድም (ዘፀአት 20፥16፣ ምሳሌ 6፥16-19፣ ምሳሌ 14፥25፣ ምሳሌ 19፥5፣ 9)። ብዙ ሰዎች ውሸቱ ጥሩ ውጤት የሚያመጣና ጉዳት የሌለው ከሆነ ሊዋሹ እንደሚችሉ ያስባሉ ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ ይህን አማራጭ አይሰጥም። የምንዋሽበት ጊዜ እንዳለ መፅሐፍ ቅዱስ አልነገረንም።
አማኞች ያለ ምንም ልዩነት እውነትን መናገር አለባቸው። እውነት ለግንኙነታችን አስፈላጊ ነው (ኤፌሶን 4፥25)።
ኤፌሶን 4፥15 ወደ መንፈሳዊ ብስለት ለማደግ እውነትን መናገር አስፈላጊ ነው ይላል።
ቆላስይስ 3፥9 ውሸት የተውነው የሃጢያት ህይወት አካል እንደሆነ ይናገራል።
እግዚአብሔር ውሸታሞችን ይቃወማል ይፈርዳልም። ውሸታሞች በእግዚአብሔር ሕግ በተፈረደባቸው አስቸጋሪ ኃጢአተኞች ዝርዝር ውስጥ ተካትተዋል (1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥10፣ ራእ 22፥15)። ውሸታሞች ሁሉ በእሳት ባሕር ውስጥ ይጣላሉ (ራእይ 21፥8)። ውሸታሞች ወደ እግዚአብሔር ከተማ አይገቡም (ራእይ 21፥27)።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ምሳሌ 11፥1 ያንብብ።
ይህ ጥቅስ የሚያወራው አንድን ነገር በክብደት ለመሸጥ ስለሚውሉ እንደ ፍራፍሬ ወይም አትክልት ወይም ስጋ ላሉ ሚዛኖች ነው። አንዳንድ ጊዜ ሰዎች ተጨማሪ ገንዘብ ለመውሰድ የውሸት ክብደት ለመስጠት የተነደፉ ሚዛኖች አሏቸው። ይህ ጥቅስ እግዚአብሔር አለመታመንን እንደሚጠላ ይናገራል።
አንድ ሰው ስለ ሁኔታው እየዋሸ ወይም ጉድለቱን እየደበቀ መሸጡ ስህተት ነው። አንድን ነገር በውድ ለመሸጥ ሲባል ሲገዙት ምን ያህል እንደከፈሉ ለአንድ ሰው ሲናገሩ መዋሸት ስህተት ነው።
አንድ ሰው ገንዘብ ላለመክፈል ሲል ስሙን እውነት ባልሆነ ነገር መፈረም ትክክል አይደለም። ሰው ለጥቅም ሲል ቀጣሪው ሰዎችን እንዲያታልል መርዳት ተገቢ አይደለም።
► የተመለከቷቸው የተለያዩ ዓይነት ታማኝነት የጎደላቸው ድርጊቶች የትኞቹ ናቸው?
መጽሐፍ ቅዱስ ክፉ ሰዎች ይበደራሉ እንጂ አይመልሱም ይላል (መዝሙረ ዳዊት 37፥21፣ ምሳሌ 3፥28)። አንዳንድ ሰዎች ተበድረዋል ከዚያም ዕዳቸውን የመክፈል ግዴታ አይሰማቸውም። መጽሐፍ ቅዱስ እኛ ከሰዎች የወሰድነውን መመለስ እንደምንችል ማረጋገጥ እንዳለብን ይናገራል (ሮሜ 13፥7-8)።
ታማኝነት ማለት የገቡትን ቃል እና ቁርጠኝነት መጠበቅ ማለት ነው። መዝሙረ ዳዊት 15 ከእግዚአብሔር ጋር ጥሩ ግንኙነት ያለውን ሰው ይገልጻል። የዚህ አይነቱ ሰው አንዱ ባህሪው ምንም ዋጋ የሚያስከፍለው ቢሆንም የገባውን ቃል መፈጸሙ ነው (መዝሙረ ዳዊት 15፥4)።
አንድ ሰው ለቀጠረው ሰው የሚገባውን ያህል ካልሠራ ታማኝነት የጎደለው ነው (ኤፌሶን 6፥5-6)።
አንድ ሠራተኛ ከአሠሪው ዕቃ ቢሰርቅ ስህተት ነው (ቲቶ 2፥9-10)።
የሆነ ነገር ከእውነቱ የበለጠ ዋጋ እንዳለው ለመናገር የውሸት ደረሰኝ መስጠት ስህተት ነው። አንድ ሰራተኛ ወይም ወኪል የተወሰነውን ገንዘብ እንዲይዝ ስለ አንድ ነገር ዋጋ መዋሸት ስህተት ነው።
ቀጣሪው የገባውን ደሞዝ ለሠራተኞች መከልከል ስህተት ነው (ያዕቆብ 5፥4)።
ሌላ ሰው ባለማወቅ ያስቀመጠውን ነገር መውሰድ ስህተት ነው። ከቻልክ ለባለቤቱ መመለስ አለብህ (ዘዳግም 22፥1)።
የሌላውን ሰው ሃብት (እንደ አሰሪ ወይም አገልግሎት) እያስተዳደሩ ከሆነ ፍቃድ ካልተሰጥዎት ገንዘብን ወይም ሌሎች ነገሮችን ለራስዎ መጠቀሙ ስህተት ነው።
በአንዳንድ ማህበረሰቦች ሰዎች በአለቃ ጥበቃ ስር ይኖራሉ። ህዝቡ ለአለቃ ታማኝ ነው እና አለቃው በሁሉም ፍላጎቶች እንዲረዳቸው ይጠበቃል። በእነዚህ ማህበረሰቦች ውስጥ ብዙ ሰዎች ብዙ የግል ንብረት የላቸውም። እንደ መሬት ያሉ በጣም አስፈላጊ ሀብቶች የማህበረሰቡ ናቸው። መሪዎች ለሁሉም ጥቅም ሲሉ ሀብቱን ማስተዳደር አለባቸው። አንድ ሰው ፍላጎት ሲኖረው ከማህበረሰቡ ሀብት የሚፈልገውን ነገር የመውሰድ መብት እንዳለው ይሰማዋል።
ተክሌ የተወለደው በጫካ መንደር ነው። ቤተሰቡ እና በዙሪያቸው ያሉ ቤተሰቦች የመንደሩ በሆነው መሬት ላይ እህልን ያመርታሉ። በጫካ ውስጥ ሀብቶችን ያገኛሉ። አንዳቸውም ቤታቸው የቆመበት ቦታ እንኳን ሳይቀር የግል መሬት አልነበራቸውም። ችግሮች ሲያጋጥሟቸው ቤተሰቦች እርስ በርሳቸው ይረዳዱ ነበር። አለቃው ለመንደሩ እንደ አባት ነበር። ህዝቡ ለፍላጎታቸው እንዲያስብ ይጠብቃሉ።
ተክሌ ወጣት በሆነ ጊዜ ጣውላን ለማምረት እንጨት በሚቆርጥ ድርጅት ውስጥ ተቀጠረ። ከሥራ ቦታው አጠገብ ለመኖር ሲል መንደሩን ለቅቆ ወጣ። በየወሩ ደሞዝ ይከፈለው ነበር። አንዳንድ ጊዜ ደሞዝ መበጀትን ስላለመደ በቂ ምግብ አይኖረውም። አለቃው ምግብ እንዲያቀርብለት ሲጠብቅ አለቃው ሁሉንም ነገር በደሞዙ መግዛቱ የተክሌ ኃላፊነት መሆኑን ሲናገር ተገረመ። የተክሌ እህት ህክምና ሲያስፈልጋት ተክሌ አለቃውን ገንዘብ ለእርሷ ይጠይቃል። አለቃው ሳይረዳው ሲቀር ተክሌ ተናደደ። ተክሌ አለቃው ለችግሮቹ ሊረዳው የሚገባ መስሎት ነበር ነገር ግን አለቃው ደሞዙ ተክሌ ብቸኛው ሀላፊነቱ እንደሆነ ተናግሯል። ተክሌ ስራውን ለቆ ሲወጣ አለቃው በበቂ ሁኔታ እንዳልረዳው ስለተሰማው ወደ መንደሩ የሚወስዳቸውን አንዳንድ መሳሪያዎች ሰረቀ።
ተክሌ ከባለቤቱ እና ከልጁ ጋር ወደ ከተማ ሄዶ በአንድ ትልቅ ግሮሰሪ ስቶር ውስጥ ሥራ አገኘ። ተክሌ ለልጁ የትምህርት ቤት ክፍያ እንዲከፍል አለቃውን ጠየቀ ነገር ግን አለቃው አላደረገውም። አንዳንድ ጊዜ ተክሌ ለቤተሰቡ የሚያስፈልገውን ነገር ሁሉ ለመግዛት በቂ ገንዘብ አላገኘም። ምግብ በሚሸጥበት ስቶር ውስጥ ይሠራ ስለነበር ከስቶሩ ምግብ ወደ ቤተሰቡ እንዲወስድ ሊፈቀድለት ይገባል ብሎ አስቦ ነበር። አለቃው እንደማይስማማ ስላወቀ በድብቅ ምግብ ይወስዳል።
አንዳንድ ሰራተኞች የአሠሪውን ቁርጠኝነት ገደብ አይረዱም። አሠሪው ለፍላጎታቸው ሁሉ ተጠያቂ ነው ብለው ያስባሉ። ለሥራቸው ከሚከፈለው ደሞዝ በተጨማሪ ብዙ ዓይነት እርዳታን ይጠይቁታል። የሚያስፈልጋቸውን ካልሰጣቸው ለመስረቅ ትክክል እንደሆነ ይሰማቸዋል ምክንያቱም የሚያስፈልጋቸውን እንዲያሟላ ዕዳ እንዳለበት ስለሚሰማቸው ነው።
► አንድ ተማሪ ለብድኑ ቲቶ 2፥9-14ን ያንብብ።
እነዚህ ጥቅሶች አንድ ሠራተኛ ከአሰሪው እንዳይሰርቅ ይነግሩናል። ቁጥር 10 ታማኝነት የክርስቶስን ትምህርት ውብ ያደርገዋል ይላል። የሚቀጥሉት ጥቂት ቁጥሮች ሰው በጸጋ ከተለወጠ የሚኖረውን ሕይወት ይገልጻሉ።
ታማኝነት ስለ ገንዘብና ንብረት ብቻ አይደለም።
አረጋዊ ለሥራ ባልደረባው ጧት 2፡00 ሰአት ላይ እንደሚገናኙ ቃል ገባ። ሆኖም ዘግይቶ ተኛ እና ቁርስ ለመብላት ጊዜ ወስዶ ከአንድ ሰአት በላይ አርፍዷል። ለሥራ ባልደረባው ሹፌሩ ዘግይቶ ሊወስደው እንደመጣ ነገረው። የሥራ ባልደረባው አልተገረመም። ሁሉም የአረጋዊ ወዳጆች ቃሉን እንደማይጠብቅ ያውቃሉ።
አረጋዊ ታማኝነት የጎደለው በሁለት መንገድ ነበር፦
1. የገባውን ቃል አልጠበቀም።
2. የዘገየበትን ምክንያት ዋሽቷል።
ሥራ እሰራለሁ ወይም በአንድ ቦታ ላይ እገኛለው ስትል ሰዎች ሊያምኑህ ይችላሉን? ይህን ስትናገር እራስህን ታምናለህን? አንድ ነገር ቃል ሲገቡ እሱን ለማሟላት አስፈላጊውን ጥረት ለማድረግም ቃል እየገቡ ነው። የገባኸውን ቃል ለመፈጸም ምንም ጥረት ከሌለ ለአንድ ነገር ቃል መግባት ስህተት ነው።
የገባኸውን ቃል ካላሟላህ ይቅርታ መጠየቅ አለብህ። ያልተሳካልህ በምን ምክንያት እንደሆነ መዋሸት የለብህም።
ለስህተትህ በድርጅትህ ውስጥ ሌሎችን መውቀስ ትክክል አይደለም። እርስዎ ስለ ስህተቶች እንደሚዋሹ ካወቁ ቡድንዎ አያምኖትም።
ታማኝ መሪ ለሰዎች እውነት ያልሆኑ ነገሮችን በመንገር ሃሳቡን እንዲከተሉ አያደርግም። Stephen Covey “መሪነት እምነትን በሚያነሳሳ መንገድ ውጤቶችን ማግኘት ነው” ሲል ጽፏል።[1]
ብዙ ሰዎች ለጓደኞች ወይም ለዘመዶች መዋሸት ስህተት እንደሆነ ያምናሉ ነገር ግን ለሌሎች የሰዎች ምድቦች መዋሸት ጥሩ ነው ብለው ያምናሉ። አንዳንድ ሰዎች ተጨማሪ ክፍያ ይገባናል ብለው በማሰብ ከአሰሪዎቻቸው ገንዘብ ወይም ቁሳቁስ ይሰርቃሉ። አንዳንድ ሰዎች ከሀብታሞች በተለይም ከውጭ ሀገር ከሚመጡ ሀብታም ሰዎች ይሰርቃሉ። አንዳንድ ሰዎች ከተለየ ጎሳ ወይም ማህበራዊ መደብ ካላቸው ሰዎች ጋር ኢፍትሃዊ ግብይቶችን ያደርጋሉ።
ኢየሱስ ባልንጀራችንን እንደ ራሳችን መውደድ እንዳለብን ተናግሯል (ማርቆስ 12፥31)። አንድ ሕግ ዐዋቂ ኢየሱስን የጠየቀውን ጥያቄ አስታውሱ? “ለመሆኑ ባልንጀራዬ ማን ነው?” (ሉቃስ 10፥29)። ሕግ ዐዋቂው ኢየሱስ ልንወደው የሚገባንን የሰዎች ምድብ እንዲገልጽ ፈልገው ነበር፣ ስለዚህም ኢየሱስ ስለ ደጉ ሳምራዊ ታሪክ ተናግሯል (ሉቃስ 10፥30-37)። ታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለ ተገናኙ የተለያየ ዘር ያላቸው ሁለት ሰዎች ነው። ከዚህ ቀደም ምንም ግንኙነት አልነበራቸውም እናም በብሄራቸው መካከል ግጭት ነበር። ሳምራዊው በምንም ዓይነት ግንኙነት ባይገደድም ችግረኛውን ረድቶታል። ኢየሱስ በዚህ ታሪክ ከተናገራቸው ነጥቦች አንዱ ማንም ሰው ከፍቅራችን መገለል እንደሌለበት ነው።
ታማኝነታችን የሚገባው ማን እንደሆነ መወሰን የለብንም። ለተመረጡ ሰዎች ብቻ ታማኝ መሆን የለብንም። አንድ ሰው በእኛ ታማኝነት የጎደለው ድርጊት እንደማይጎዳ ብናስብም በታማኝነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት እንፈልጋለን (ሐዋርያት ሥራ 24፥16፣ በተጨማሪም ፊልጵስዩስ 1፥10፣ 2ኛ ቆሮንቶስ 5፥9ን ተመልከት)።
ምን አይነት ሰው መሆን ትፈልጋለህ? እግዚአብሔር ምን ዓይነት ሰው እንድትሆን ይፈልጋል?
አንድ ሰው ያንተ ስነምግባር ላይገባው ይችላል ነገር ግን እግዚአብሔር ስነምግባር ያለው ሰው እንድትሆን ይፈልጋል። አንድ ሰው የአንተ ታማኝነት አይገባው ይሆናል ነገር ግን እግዚአብሔር ታማኝ ሰው እንድትሆን ይፈልጋል። አንድ ሰው ያንተ ፍቅር ላይገባው ይችላል ነገር ግን እግዚአብሔር በማይገባህ ጊዜ ወዶሃል እና እግዚአብሔር አፍቃሪ ሰው እንድትሆን ይፈልጋል።
► ተማሪዎች ለቡድኑ 1ኛ ጴጥሮስ 2፥21-23 እና 1ኛ ጴጥሮስ 3፥8-12 ማንበብ አለባቸው።
የሌሎች ባህሪ ባህሪዎን እንዲወስን አይፍቀዱ። ሰው ሊዋሽህ ይችላል ነገር ግን ውሸታም መሆን የለብህም። ሰው ሊሰርቅህ ይችላል አንተ ግን ሌባ መሆን የለብህም። አንድ ሰው ላንተ ባለጌ ሊሆን ይችላል ነገር ግን አንተ የአክብሮት ሰው መሆን አለብህ።
በዚህ ክፍል ውስጥ ያሉት ገለፃዎች ሁሉም እውነተኛ ጉዳዮች ናቸው ግን ስሞች እና ዝርዝሮች ተለውጠዋል። እነርሱ የስርቆት ወይም የውሸት ወይም የሁለቱም ምሳሌዎች ናቸው።
ማስታወሻ ለክፍል መሪ፡ ተማሪዎች በእያንዳንዱ ገለፃዎች ላይ የሆነውን ነገር መረዳታቸውን ያረጋግጡ። በገለፃው ላይ ያለው ድርጊት ለምን ስህተት እንደሆነ ተማሪዎች እንዲያብራሩ ይጠይቁ።
1. አለሙ በፋብሪካ ውስጥ ሰርቷል። ፋብሪካው ሊተካቸው እንደሚችል ስለሚያውቅ ብዙ ጊዜ የቤት ማጽጃ ቁሳቁሶችን፣ መሳሪያዎችን እና ትናንሽ እቃዎችን ወደቤቱ ይወስድ ነበር።
2. አስራት የአንድ ትልቅ ድርጅት የጭነት መኪና ሹፌር ነበር። አንዳንድ ጊዜ የኩባንያውን መኪና ሲነዳ በመንገድ ዳር “ነዳጅ እንገዛለን” የሚል ምልክት ያያል። አንዳንድ ጊዜ መኪናውን አቁሞ ትንሽ ነዳጅ ከመኪናው ይሸጥላቸዋል በዚህም ድርጅቱ ትንሽ መጠን መወሰዱን እንደማያውቁ ያስባል።
3. ወርቅነሽ ለምትሰራበት መስሪያ ቤት የኮምፒዩተር መሳሪያዎችን እንድትገዛ ያምኑዋት ነበር። ገንዘቡን የተወሰነውን እንድትይዝ ከፍተኛ የግዢ ዋጋ የሚያሳይ ደረሰኝ እንዲጽፍ በመደብሩ ውስጥ ላለው ሻጭ ጉቦ ሰጠችው።
4. በአንድ ትልቅ ከተማ ውስጥ በሚገኝ መናፈሻ ውስጥ የተቃጠሉ አምፖሎችን የሚሸጥ ሰው አለ። የሚገዙት ሰዎች አምፖሎቹ እንደማይሠሩ ያውቃሉ። ጥሩ አምፖሎችን ወደሚሰርቁበት ወደ ቢሮአቸው ለመውሰድ ይገዙዋቸዋል በአሮጌ አምፖልም ይተኳቸዋል።
5. ሀይሌ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ነበር። አንድ ቀን የአንድ ተማሪ አባት ወደ እርሱ መጥቶ ልጁ በአልጀብራ ጥሩ ውጤት እንዲያገኝ ጠየቀው። ለሃይሌ ገንዘብ ሰጠው። ሀይሌ የአልጀብራ መምህሩ ለተማሪው ጥሩ ውጤት እንዲሰጠው አዘዘው።
6. መኮንን የዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር ነበር። ደመወዙ ትንሽ ነበር። ፈተናው በጣም ከባድ እንደሚሆን እና ማንም ተማሪ መልሱን የያዘ ገፅን ከእርሱ ሳይገዛ በፈተናው ጥሩ ውጤት እንደማያገኝ ለክፍሉ ተናገረ።
7. ተስፋዬ የመንግስት ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ነበር። አንድ ቀን በሚስዮን ድርጅት ውስጥ የሚሠራው ጓደኛው ሃይሉ፣ ሚሲዮኑ በትምህርት ቤቱ ህንፃ ውስጥ የተወሰኑ ክፍሎችን መከራየት ይችል እንደሆነ ጠየቀ። ተስፋዬ ዋጋ ሰጠ እና ኃይሉ ገንዘቡን ለተስፋዬ በየወሩ ያመጣል። ተስፋዬ ገንዘቡን አስቀምጦ ገቢውን አላሳወቀም።
8. ሃይሉ ለክፍሎች የተወሰነ ቦታ መከራየት ለሚያስፈልገው ሚሲዮኑ ሰርቷል። ኃይሉ የትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር ወደሆነው ጓደኛው ተስፋዬ ጋር ሄደ። በኪራይ ዋጋ ላይ ተስማምተዋል ከዚያም ሃይሉ ለሚሲዮኑ ከፍተኛ መጠን ነገራቸው። ኃይሉ በየወሩ ገንዘቡ ለተስፋዬ ቢያደርስም ተጨማሪውን መጠን ይይዝ ነበር።
9. ደረጄ አዲስ ሕንፃ ለሚያስፈልገው አገልግሎት ሰርቷል። አገልግሎቱም ለደረጄ የሚገነባላቸው የኮንስትራክሽን ኩባንያ ፈልጎ እንዲያገኝ ነግረውታል። ደረጄ ከብዙ የግንባታ ኩባንያዎች ጋር ተነጋገረ። ጥሩ ዋጋ የሚሰጠውን ኩባንያ ከመምረጥ ይልቅ ከአገልግሎት ካገኙት ገንዘብ የተወሰነውን እንደሚሰጠው ቃል የገባለትን መረጠ።
10. አለማየሁ ለመኪናው ፍቃድ መስጠት አስፈልጎት ነበር ነገር ግን አንዳንድ መብራቶች ስላልሰሩ ፍተሻ እንደማያልፍ ያውቅ ነበር። መኪናውን ወደ ፍቃድ መስጫ ክፍል ወሰደ እና መኪናቸውን ለማስመርመር እና ፍቃድ ለመውሰድ ብዙ ሰዎች ተሰልፈው ተመለከተ። ከበሩ አጠገብ ያለ ሰው በዋጋ ያለ ምንም ምርመራ ፈቃዱን በፍጥነት እንደሚያገኝ ነገረው። አለማየሁ ዋጋ ከፍሎ ብዙም ሳይቆይ ፈቃዱን ይዞ ወደ ቤቱ ሊሄድ ቻለ።
11. ዮሴፍ መኪናውን ከመኪና ማቆሚያ ቦታ ሊወስድ መጣ። የመኪና ማቆሚያ አስተናጋጁ የማቆሚያ ዋጋውን ነገረው። ዮሴፍ ለአስተናጋጁ ዝቅተኛ ገንዘብ የከፈለ ቢሆንም የመኪና ማቆሚያ ትኬቱን አስቀምጦ ለሌላ ደንበኛ እንዲሰጥ ነገረው እንዲሁም አስተናጋጁ ዮሴፍ የከፈለውን ገንዘብ እንዲጠቀም አደረገ።
12. ሳራ ለፈተና በቂ ጥናት አላደረገችም። ወደ ክፍል ስትመጣ ከጓደኛዋ ፈተና ምላሾችን መቅዳት እንድትችል ጎበዝ ተማሪ ከሆነች ጓደኛዋ አጠገብ ተቀመጠች።
13. ጊዮርጊስ ለትልቅ የመንግስት እርሻ ማረሻ የሚጎትት ትራክተርን ነድቷል። ቀደም ብሎ መጨረስ ፈልጎ ነበር። ማረሻው በጥልቀት እንዳይቆፈር በማንሳት ትራክተሩን በፍጥነት እንዲነዳው አደረገ። ማሳው የተዘጋጀ ቢመስልም በአግባቡ ስላልታረሰ ጥሩ ምርት አልሰጠም።
14. ፓስተር አብርሃም ቤተክርስቲያንን በመጋቢነት እንዲያገለግል በሚስዩን ተልኳል። ሚስዮኑ ወርሃዊ ደሞዝ ይልክለታል። ፓስተር አብርሃም ቤተክርስቲያኗም እንድትከፍለው ስለፈለገ ሚስዮኑ እንደማይደግፈው ለቤተክርስቲያኑ ሰዎች ነገራቸው።
15. አንድ ሌባ ወደ ሰናየት ቤት ገብቶ ገንዘብ ሰረቀ። ስለ ጉዳዩ ለጓደኞቿ ስትነግራቸው ሌባው ያልወሰዳቸውን ሌሎች ነገሮችን እንደወሰደ ተናገረች። ጓደኞቿም በዚህ አዝነው እና የተሰረቀች መስሏቸው ያንንም ለመተካት ገንዘብ ሰጧት።
16. መሃሪ የአንድ ትንሽ መንደር አለቃ ነበር። በመንደሩ ቤተክርስቲያን መሪም ነበር። የእርሱ ሰዎች ጥንታዊ፣ ያልተማሩ እና ድሆች ነበሩ፣ ነገር ግን መንደሩ ብዙ መሬት ነበረው። የከተማዋ ነጋዴዎች ለእርሻ ሥራ የሚሆን መሬት እንዲገዙ ጠየቁ። መሃሪ የመንደሩን መሬት በሙሉ ሸጦ በገንዘቡ በከተማው ውስጥ ለራሱ ቤት ሠራ።
17. በየአመቱ የክብር ፀጋ ማህበረሰብ ቤተክርስቲያን “የዓመቱ ምርጥ እናት” በማለት እናት ይመርጣሉ። ፍቅርተን የመረጡት ለእናት ጥሩ ምሳሌ ስለነበረች ሳይሆን ለቤተክርስቲያን መዋጮ እንደምታደርግ ስለሚያውቁ ነው። ከመረጧትም በኋላ ፍቅርተ ለንብረቱ የሚሆን አዲስ በሮች ለመግዛት ለቤተክርስቲያኑ ገንዘብ ሰጠች። በሚቀጥለው ዓመትም ቤተክርስቲያንኗ ፍቅርተ ወደ ሌላ ከተማ ብትሄድም እንደገና “የዓመቱ ምርጥ እናት” እንድትሆን ወሰነች።
18. ሚካኤል ለአንድ የአገልግሎት ተቋም ሹፌር ነበር። ሁል ጊዜ ምሽት የአገልግሎቱን መኪና ይዞ ወደ ፖርክ ደህንነቱ በተጠበቀ ቦታ ለማቆም ይሄድ ነበር። አንዳንድ ጊዜ መኪናውን ከማቆሙ በፊት ተሳፋሪዎችን ለማጓጓዝ ወይም ለደንበኞቹ ጭነት ይጠቀምበት ነበር።
ይህ ታሪክ ልቦለድ ነው ግን በብዙ ቦታዎች የሆነውን ነገር ይገልጻል።
ሸኮ ከተማ የሚኖሩ አማኞች በሚቀጥለው ዞን ውስጥ በድህነት የሚኖሩ ብዙ ሰዎች እንዳሉ አወቁ። የዚያ ዞን ሰዎች ኩምብቾ የሚባል ጎሳ ነበሩ። ለብዙ ትውልዶች የጋምቤላ ሰዎች ብዙ የሕክምና እንክብካቤ እና ትምህርት ሳያገኙ በጥንታዊ ቤቶች ውስጥ ይኖሩ ነበር። ብዙዎች በቂ ምግብ አልነበራቸውም እና አንዳንዶቹ ለረሃብ ተዳርገዋል።
የወላይታ አማኞች ጋምቤላዎችን ለመርዳት ገንዘብ መስጠት ጀመሩ። መዋጮ ለመጠየቅ ወደ ሌሎች አውራጃዎች ወደሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ተወካዮችን ልከዋል።
በወላይታ ያሉ አማኞች የምግብ ጭነት መኪናዎችን ወደ ጋምቤላ መላክ ጀመሩ። ምግቡን ለማከፋፈል በጋምቤላ ቤተክርስቲያን መሪዎች ላይ ጥገኛ ነበሩ።
የጋምቤላ መሪዎች ምግቡን ለህዝባቸው ለመሸጥ ገበያ አቋቋሙ። ገንዘብ ያላቸው ሰዎች ብቻ ሊገዙት ይችላሉ ስለዚህ አንዳቸውም ምግብ ለረሃብተኞች አልደረሰም። የቤተክርስቲያን መሪዎች እና ጓደኞቻቸው ትርፉን ወስደዋል። የተወሰኑት ምግቦች ሰዎች የበለጠ መክፈል በሚችሉበት ወደ ሌላ ዞን ለመሸጥ ተልኳል።
የወላይታ አማኞች ምግቡ በጣም ለሚያስፈልጋቸው ሰዎች በነጻ መሰጠት እንዳለበት አጥብቀው ጠየቁ። የጋምቤላ አብያተ ክርስትያናት መሪዎች ለስርጭቱ በጀት አዘጋጅተው መኪናዎችን ከአሽከርካሪዎች ጋር መከራየት እና ሰዎችን ለእርዳታ ክፍያ መክፈልን ያካትታል። ዋጋቸውን ከመደበኛው ዋጋዎች ከፍ አድርገው ያስቀምጣሉ እና ተጨማሪውን ገንዘብ ይወስዳሉ። የወላይታ አማኞች የወጪውን ሪፖርት ሲጠይቁ ጋምቤላዎች የውሸት ዘገባዎችን ጻፉ።
የወላይታ አማኞች ታማኝነት የጎደላቸውን ድርጊቶች ባገኙ ቁጥር ተበሳጭተው በዚህም ተነሳሽነታቸውን አጥተዋል። እነርሱን ለመርዳት ሌሎች የጋምቤላ መሪዎችን ለማግኘት ሞክረው ነበር ነገር ግን ተመሳሳይ ችግሮች አጋጥሟቸው ነበር። ብዙ የወላይታ አማኞች መስጠት አቁመዋል። አንዳንዶች መስጠት ቀጠሉ። በወላይታ ድጋፍ ምክንያት ጥቂት የጋምቤላ ፓስተሮች ብዙም ሳይቆይ መኪናዎች እና ጥሩ ቤቶች ነበሯቸው። ሌሎች ፓስተሮች ይቀኑባቸው እና ከወላይታ ሰጭዎች ጋር ግንኙነት ለመፍጠር ይመኛሉ። ራቅ ባሉ አካባቢዎች የሚኖሩ አብዛኞቹ የተራቡ ሰዎች እርዳታ አላገኙም።
Warren Buffet፤ Berkshire Hathaway የተባለ ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ነበር። በWalmart ባለቤትነት የተያዘውን McLane Distribution የተባለ ኩባንያ መግዛት ፈለገ። ግዢው 23 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ነበር። በተለምዶ ይህ ግዢ ገዢው ሁሉንም ነገር ማረጋገጥ እንዲችል ለወራት ፍተሻ ያስፈልገዋል። Buffet ከWalmart መሪዎች ጋር ተገናኝቶ በአንድ ስብሰባ ላይ ስምምነት አደረገ። ንብረቶቹ እና ሌሎች ቁሶች ደህና መሆናቸውን ለማረጋገጥ ማንንም አልላከም። በኋላም “ሁሉም ነገር Walmart እንደተናገረው እንደሚሆን አውቀናል እናም ነበር” አለ። መሪዎቹ እርስ በርሳቸው ስለሚተማመኑ ይህ ግዙፍ ስምምነት በፍጥነት ተጠናቀቀ።[1]
አሁን በቀደሙት ገለፃዎች ላይ ስለተገለጹት ሰዎች አስብ። አንዳቸውም ቢሆኑ እንደዚህ ያለ ስምምነት ማድረግ አይችሉም ምክንያቱም እነርሱ እምነት የሚጣልባቸው አይደሉም። ሁሉም ነገር መፈተሽ አለበት ይህም ብዙ ጊዜ እና ወጪ ይጠይቃል።
► በባህልዎ ውስጥ ሰዎች ለማስወገድ የሚከብዱዋቸው አንዳንድ ታማኝነት የጎደላቸው ድርጊቶች የትኞቹ ናቸው?
► መለወጥ የሚያስፈልግዎ አሠራር ምንድን ነው?
የሰማይ አባት
የጽድቅና የእውነት አምላክ ስለሆንክ እናመሰግንሃለን። ከእኛ ጋር በምታደርገው ግንኙነት ሁል ጊዜ እውነተኛ ስለሆንክ እናመሰግናለን።
ለእኛ ያለህን የታማኝነት መስፈርት እንድንከተል እርዳን። በምንናገረው እና በምናደርገው ነገር ሁሉ የታማኝነትን መርሆችን እንድንጠቀም እርዳን።
የሚያቀርብልን እና የሚመራን አባታችን ስለሆንክ እናመሰግናለን። እንድትንከባከበን ልናምንህ እንፈልጋለን።
አሜን
(1) ስለ እያንዳንዳቸው ስለሚከተሉት አንድ አንቀጽ ጻፍ፦
በእግዚአብሔር ባህሪ (እውነት) እና እግዚአብሔር ለእኛ ባለው መስፈርት (ታማኝነት) መካከል ያለውን ግንኙነት አብራራ። እግዚአብሔር በምንናገረው እና በምናደርገው ሁሉ ታማኝ እንድንሆን የሚፈልግበትን ምክንያት ግለጽ።
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ታማኝነት የሚናገረውን ጠቅለል አድርገህ ጻፍ። በማጠቃለያህ ውስጥ ቢያንስ ሦስት የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችን ተጠቀም።
ታማኝ አለመሆን/መሆን ከሌሎች ጋር ባለን ግንኙነት ላይ ተጽእኖ የሚያሳድርበትን ቢያንስ አራት መንገዶችን አስረዳ።
(2) በባህልዎ ውስጥ ካሉ ሰዎች ጋር ልታካፍለው የምትችለውን ስለ ታማኝነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ፕረዘንቴሽን አዘጋጅ። ለእግዚአብሔር መስፈርት መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ስጥ ከዚያም በተወሰኑ ሁኔታዎች ላይ ተግባራዊ አድርግ።
13 lessons · አማርኛ
Your print request has been recorded. Your download should begin shortly.
Download Print-Ready FileFree to print for ministry use. No changes to content, no profit sales.
SGC exists to equip rising Christian leaders around the world by providing free, high-quality theological resources. We gladly grant permission for you to print and distribute our courses under these simple guidelines:
All materials remain the copyrighted property of Shepherds Global Classroom.
Questions? info@shepherdsglobal.org
Total
$21.99Added to Cart!
By submitting your contact info, you agree to receive occasional email updates about this ministry.
Download audio files for offline listening
No audio files are available for this course yet.
Check back soon or visit our audio courses page.
Share this free course with others